Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Thursday
Aug 28th
Home arrow Sections arrow በአየር ንብረት ለውጥ...
በአየር ንብረት ለውጥ... Print E-mail
Sunday, 13 January 2008

በአየር ንብረት ለውጥ ሴቶች የበለጠ ተጠቂ ናቸው

በእስያ የዓለም ሙቀት መጨመር የሚያስከትለውን ተጽዕኖ በተመለከተ ጥናት ያከናወነ አካባቢና የልማት ባለሙያዎች ቡድን በአየር ንብረት ለውጥ የበለጠ ተጠቂ የሆኑት ሴቶች መሆናቸውን አመልክቷል፡፡


ጥናቱ እንዳለው በማኅበረሰቡ ውስጥ ሴቶች ተሰሚነት የሌላቸውና ዋነኛ ሚና የሚጫወቱ በመሆናቸው በሴቶች የሚመሩ ቤተሰቦች የአየር ንብረት ለውጥ ፈተና ሆኖባቸዋል፡፡

እንደ ጥናት ቡድኑ የዚህ ምክንያቶች ብዙ ሲሆኑ ሴቶች የኢኮኖሚ ጫና ያለባቸውና ሁሉንም ኃላፊነት የሚሸከሙ መሆናቸውና ወንዶች ጥለዋቸው የሚሄዱበት አጋጣሚም ስለሚኖር የአየር ንብረት ለውጥ የሚያመጣውን ፈተና ብቻቸውን ለመጋፈጥና ለመቋቋም አይችሉም፡፡

በአየር ንብረት ለውጥ ውጤቶች በድርቅና በጎርፍ፣ በደን መመናመን ምክንያት ሴቶች ማገዶ ፍለጋ ያሉ ተግባራት ለሴቶች አስቸጋሪ ይሆናሉ፡፡

በዚህ ረገድ የአየር ንብረት ለውጥ በሴቶች ላይ የሚያደርሰው ተጽዕኖ በተመለከተ የአገራት መንግስታትና ፖሊሲ አውጪዎች ትኩረት ሰጥተው ጥናቶች ሊያደርጉ እንደሚገባ ቡድኑ አስተያየት መስጠታቸውን ኢንዶ-ኤዥያ ዜና አገልግሎት ዘግቧል፡፡

 
< Prev   Next >