Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Sunday
Sep 07th
Home arrow Sections arrow የንግድ ባንክ ባለሙያዎች የመንግሥትን...
የንግድ ባንክ ባለሙያዎች የመንግሥትን... Print E-mail
Wednesday, 16 July 2008

የንግድ ባንክ ባለሙያዎች የመንግሥትን ፖሊሲና ስትራቴጂ እያጠኑ ነው

 

በጋዜጣው ሪፖርተር

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባለሙያዎች በመንግሥት ፖሊሲና ስትራቴጂ ላይ ያተኮረ የ16 ቀናት ሥልጠና ጀመሩ፡፡

 

ከሐምሌ 7 ቀን 2000 ዓ.ም ጀምሮ ሲኤምሲ አካባቢ በሚገኘው የኢትዮ ቻይና ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ እየተካሄደ ባለው ሥልጠና ላይ የባንኩ ከፍተኛ ባለሙያዎች መሳተፋቸውን ምንጮቻችን ተናግረዋል፡፡

የባንኩ ባለሙያዎች በዚሁ ሥልጠና ላይ የኢፌዴሪ የውጪ ጉዳይና የአገራዊ ደህንነት ፖሊሲና ስትራቴጂ፣ የኢፌዴሪ የኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጂ፣ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ጉዳዮች ስትራቴጅ፣ የገጠር ልማት ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ስልቶች፣ የኢፌዴሪ መንግሥት የማስፈፀም አቅም ግንባታ ስትራቴጂና ፕሮግራም በሚሉት ርዕሶች ላይ ትምህርትና የቡድን ውይይቶች ይካሄዳሉ፡፡

ቀደም ብሎ ባንኩ ባሳወቀው ፕሮግራም መሰረት ሥልጠናው ለ11 ቀናት ይካሄዳል ከተባለ በኋላ ወደ 16 ቀናት መራዘሙ እንደተነገራቸው ምንጮቻችን ጠቁመዋል፡፡

የንግድ ባንክ ሐምሌ 2 ቀን 2000 ዓ.ም በአቶ ሰይፉ ቦጋለ ፊርማ ለሠራተኞቹ ይፋ ባደረገው የሥልጠና መግለጫ ላይ እንደተመለከተው በሥልጠናው ሂደት ተሳታፊዎች ንቁ ተሳትፎ ማድረጋቸውን ለመመዘን በዚህ ጉዳይ በተሰየሙ ገምጋሚዎች በምልከታ እና የቡድን ግምገማ እንደሚካሄድ በመጨረሻም በውጪ አካላት የፅሑፍ ፈተና እንደሚሰጥ ጠቁሟል፡፡

የፌዴራል መንግሥት የሲቪል ሰርቪስ አገልጋዮች (የመንግሥት ሰራተኞች) የመንግሥትን ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ጠንቅቀው ሊያውቁ ይገባል የሚል አቋም ከያዙ በኋላ ይህንኑ ለማውሳት ለተለያዩ መ/ቤቶች ሰራተኞች ተመሣሣይ ሥልጠና ሲሰጥ መቆየቱ ይታወሳል፡፡

የዚህ ዓይነቱ ሥልጠና ከገዥው ፓርቲ ፖለቲካ ጋር በቀጥታ በማስተሳሰር ተገቢ አለመሆኑን የሚተቹ አንዳንድ ወገኖች መኖራቸውም አይዘነጋም፡፡
 
< Prev   Next >