Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Thursday
Aug 28th
Home arrow Sections arrow ያላለቁላቸው የቆዳ ምርቶች የሚልኩ...
ያላለቁላቸው የቆዳ ምርቶች የሚልኩ... Print E-mail
Wednesday, 16 January 2008

ያላለቁላቸው የቆዳ ምርቶች የሚልኩ ላይ ታክስ ሊጨመር ነው

በኢትዮጵያ በቆዳ ሌጦ ማምረት ሥራ ላይ የተሰማሩ ኩባንያዎች ያለቀላቸውን ምርቶች እንዲልኩ ለማስቻል የተረቀቀው አዲስ ሕግ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት መቅረቡ ተገለፀ፡፡ ሕጉ ያላለቀላቸውን የቆዳና የሌጦ ምርቶች ላለቀላቸው ምርቶች በመተካት የተሻለ ገቢ ለማግኘት እንዲያስቸል ታስቦ እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡

መንግሥት የአገር ውስጥ የቆዳና የሌጦ አምራሮች ያለቀላቸውን የቆዳና የቆዳ ውጤት የሆኑ ምርቶችን በብዛት ለመላክ እንዲችሉ ለማድረግ ታስቦ የተዘጋጀ ሕግ እንደሆነ ከንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትር ያገኘነው መረጃ ያስረዳል፡፡

ያነጋገርናቸው የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ባለሙያ እንደገለፁት በቆዳና በቀዳ ውጤቶች አምራች በሆኑ ኩባንያዎች ላይ ተግባራዊ የሚሆነው ይህ በዋናነት ያላለቀላቸው የቆዳና የሌጦ ምርቶችን ወደ ውጪ የሚልኩት ላይ የታክስ ክፍያን የሚያሳድግ እንደሆነ ታውቋል፡፡

እስካሁን ባለው አሰራር ያላለቀለት የቆዳ ምርቶችን የሚልኩት ፋብሪካዎች የሚጣልባቸው ቀረጥ አነስተኛ እንደነበር ያመለከተው መረጃ አሁን ግን ከዘርፉ ከፍተኛ የሆነ የውጭ ምንዛሪ ለማግኘት ያለቀላቸውን ምርቶች መላክ ተገቢ በመሆኑ መንግሥት ይህንን እርምጃ ሊወስድ መገደዱን ያመላክታል፡፡

መንግሥት ይህንን ሕግ ተግባራዊ ከማድረጉ በፊት በከፊል ያለቀለትና ያላለቀለት የቆዳ ምርት ወደ ውጭ ለሚልኩ ኩባንያዎች ያለቀለት ምርት ወደውጭ እንዲልኩ ለማስቻል አቅማቸውን እንዲገነቡ ጊዜ ሰጥቷቸው እንደነበር ታውቋል፡፡

በአሁኑ ጊዜ ይህ የተሰጣቸው የጊዜ ገደብ በመጠናቀቁ ያላለቀላቸው የቆዳ ምርቶች በሚልኩ ኩባንያዎች ላይ የሚጣለውን ታክስ ከፍ የሚያደርገው ረቂቅ ሕግ ወደ ሚኒስትሮች ምክር ቤት እንዲላክ የተደረገ መሆኑንና ረቂቁም ያዘጋጀው የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር መሆኑ ታውቋል፡፡

ይህ ማለት ግን ያላለቁላቸው የቆዳ ምርቶች ለውጭ ገበያ አይቀርቡም ማለት እንዳልሆነ እኚሁ ባለሙያ ገልፀዋል፡፡ የሕጉ ዋነኛ አላማ ያላለቀላቸውን የቆዳ ምርቶች ወደ ውጭ የሚልኩ ኩባንያዎች እንዳይበረታቱ ለማድረግና ትኩረታቸውን ወዳለቀለት የቆዳና የቆዳ ውጤቶች እንዲያደርጉ ለማድረግ እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡ 

 
< Prev   Next >