| ፋልኮን የተባለ የእንግሊዝ ኩባንያ... |
|
|
| Wednesday, 06 August 2008 | |
|
ፋልኮን የተባለ የእንግሊዝ ኩባንያ የነዳጅ ፍለጋ ስምምነት ነገ ይፈራረማል
በቃለየሱስ በቀለ የፌዴራል ማዕድንና ኢነርጂ ሚኒስቴርና ፋልኮን የተባለ የእንግሊዝ ኩባንያ በነዳጅ ፍለጋና ልማት ስምምነት ላይ ነገ ይፈራረማሉ፡፡ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት በጣና ዙሪያ የነዳጅ ፍለጋ ለማካሄድ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ጋር ድርድር ሲያደርግ መቆየቱን፣ የነዳጅ ፍለጋና ልማት ፈቃድ ለማግኘት ለሚኒስተሮች ምክር ቤት ቀርቦ በቅርቡ መጽደቁን ምንጮች ለሪፖርተር ጋዜጣ ገልፀዋል፡፡ ስምምነቱን የማዕድንና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ አለማየሁ ተገኑና የኩባንያው ኃላፊ (ተወካይ) በነገው ዕለት ይፈራረማሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ምንጮቹ ገልፀዋል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ነዳጅ ይገኝባቸዋል ከሚባሉት አምስቱ ቦታዎች (ሴዲመንተሪ ቤዚን"፣ ጋምቤላ፣ ኡጋዴን፣ ኦሞ፣ አባይሸለቆ፣ ትግራይና አፋር አካባቢዎች መካከል ጣና ዙሪያ አንዱ መሆኑን ምንጮቹ ገልፀዋል፡፡ |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Forums |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Contact Us |