Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Thursday
Aug 28th
Home arrow Sections arrow ለዘመናዊ ፍሳሽ ማስወገጃ ሥራ...
ለዘመናዊ ፍሳሽ ማስወገጃ ሥራ... Print E-mail
Wednesday, 06 August 2008

ለዘመናዊ ፍሳሽ ማስወገጃ ሥራ የ282 ሚሊዮን ብር ስምምነት ተፈረመ

የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኘሮጀክት ከ25ዐ ሺ ያላነሱ ነዋሪዎችን የዘመናዊ ፍሳሽ ማስወገጃ ተጠቃሚ የሚያደርግ የ282 ሚሊዮን ብር ስምምነት ከቻይናው ሲ.አር.ቢ.ሲ ጋር ተፈራረመ፡፡

 

ከተማው ከአምስት ሳይቶች ለተሰሩት የጋራ መኖሪያ ቤቶች መካከል ለገላን ቦሌ አያት ሳይት፣ ጆሞ፣ ጐተራና ጐፋ ለተባሉት የጋራ ቤቶች ሳይት የፍሳሽ ማስወገዳቸውን የአዲስ አበባ ከተማ ውሃና የፍሳሽ ማስወገጃ የማገናኘት ሥራ ኩባንያው እንደሚሰራ ተገልጿል፡፡

(ኢዜአ)

                                         
እናትና ልጅ በውሃ ተወስደው ሞቱ

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ምንጃር ሸንኮራ ወረዳ እናትና ልጅ በደራሽ ውሃ ተወስደው መሞታቸውን የዞኑ ፖሊሲ መምሪያ አስታወቀ፡፡

በእናትና ልጅ ላይ አደጋው የደረሰው እናት የቄሮ ገልፎ ወንዝን በመሻገር ከወንዙ ማዶ ከብት ይጠብቅ የነበረውን ልጃቸውን ለማምጣት በመሻገር ላይ እንዳሉ በድንገት በተከሰተ ደራሽ ውሃ ሲሆን፣ የአካባቢው ህብረተሰብ ከፖሊስ ጋር በመተባበር የሟቾቹን አስክሬን በመፈለግ ላይ መሆኑን ገልጿል፡፡

(አዲስ ዘመን ሐምሌ 28 ቀን 2ዐዐዐ ዓ.ም".

                                         
የእንቅርት በሽታ እናቶችንና ህፃናትን እያጠቃ ነው

በቄለም ወለጋ ዞን በርካታ እናቶችና ሕፃናት በእንቅስር በሽታ እንደሚጠቁ ነዋሪዎች አመለከቱ፡፡ የዞኑ ጤና መምሪያ በሽታውን ለመከላከል የበኩሉን ጥረት እያደረገ መሆኑን ገልጿል፡፡

በሽታው በተለይ እናቶችና ሕፃናት ለእንቅርት በሽታ የሚጋለጡት ከጐረቤት ሀገር በህገ ወጥ መንገድ የሚገባውንና በአካባቢው የሚመረተውን አዮዲን የሌለው ጨው ስለሚጠቁሙ መሆኑን፣ በሽታው ጐልቶ የሚታየው በዞኑ አንፊሎና ጊዳሚ ወረዳዎች መሆኑን አስታውቋል፡፡ የዞኑ ጤና ጣቢያም ችግሩን ለማቃለል በተደረገው ጥረት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ138 ሺ ለሚበልጡ እናቶችና ሕፃናት የአዮዲ ካፕሱል ሕክምና መሰጠቱን ገልጿል፡፡

(ኢዜአ)

                                         
በጐባና ሮቤ ሕገ ወጥ የነዳጅ ሽያጭ እየተካሄደ ነው


በባሌ ዞን ለጐባሩ ሮቤ ከተማ የሚገኙ የነዳጅ ማደያዎች ሕገወጥ የነዳጅ ሽያጭ ላይ በመሰማራታቸው የትራንስፖርት ዋጋ በከፍተኛ ዋጋ መጨመሩን የከተሞቹ ነዋሪዎች ገለፁ፡፡

ማደያዎቹ መንደር ውስጥ በህገወጥ መንገድ ነዳጅ ለሚቸረችሩ ግለሰቦች፣ ነዳጅ በበርሜል ስለሚሸጡ፣ ነዳጅ ባራገፉ ማግስት ጨርሰናል ይላሉ፡፡ አንድ ሊትር ናፍጣ ከህገወጦቹ ቸርቻሪዎች በ13 ብር እንደሚገዙ ገልፀዋል፡፡

(ኢዜአ)

                                         
የኔዘርላንድ መንግሥት ተጨማሪ እርዳታ ሰጠ

የኔዘርላንድ መንግሥት በድርቅ ለተጐዱ ወገኖች መርጃ የሚሆን ቀደም ብሎ ሰጥቶት ከነበረው 8.5 ሚሊዮን ዩሮ በተጨማሪ አምስት ሚሊዮን ዩሮ ሰጠ፡፡

እርዳታው ሙሉ በሙሉ ለሰብአዊ እርዳታው የሚውል መሆኑንና፣ ለምግብ ለህክምናና ለንፁህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት እንደሚውል ተገልጿል፡፡

(ጋዜጣዊ መግለጫ)
 
< Prev   Next >