Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version

Tuesday
Dec 02nd
Home arrow Sections arrow አህመድ ያሲን መንግሥት ለችግራችን...
አህመድ ያሲን መንግሥት ለችግራችን... E-mail
Sunday, 28 September 2008
አህመድ ያሲን መንግሥት ለችግራችን መፍትሄ ይፈልግልን አሉ

በደረጀ ጠገናው

በፊፋ ዕውቅና የተነፈገው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከቀድሞ አመራር ጋር የተፈጠረውን ውዝግብ ለመፍታት መንግሥት ጣልቃ እንዲገባ ጥሪ አቀረበ፡፡

አቶ አህመድ ያሲን የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት በተለይ ለሪፖርተር ጋዜጣ ዓርብ ዕለት በጽ/ቤታቸው በሠጡት ቃለምልልስ እንዳስታወቁት በፌዴሬሽኑ በአሁኑ ወቅት የተፈጠረው ችግር የአገር ጉዳይ መሆኑን፣ ችግሩ ለእግር ኳስ ዕድገት አሉታዊ ተፅዕኖ ከማስከተሉ በተጨማሪ የአገሪቱ አንጡራ ሀብት ለብክነት እየዳረገ በመሆኑ መንግሥት በጉዳዩ ገብቶ ፖለቲካዊ ውሣኔ ሊሰጥበት ይገባል፡፡

መንግሥት ይግባ ሲባል መንግሥት በስፖርቱ ውስጥ ጣልቃ ይግባ ማለታችን አይደለም የሚሉት አቶ አህመድ ለብሔራዊ ጥቅም ሲባል በዓለም አቀፉ እግር ኳስ ማኅበር የተጣለብንን ቅጣት ለመቀልበስ በሕጋዊና ዲፕሎማሲያዊ መንገድ የምናደርገው ትግል እንደተጠበቀ ሆኖ መንግሥት የገጠመንን ችግር ዝም ማለት አይገባውም ብለዋል፡፡

ፌዴሬሽኑ የፊፋ እገዳ በመቃወም ችሎታ ያላቸው ጠበቃ ቀጥሮ ጉዳዩን ወደዓለም አቀፉ የስፖርት ግልግል ፍ/ቤት (ካስ) መውሰዱንም አቶ አህመድ ተናግረዋል፡፡ (ከአቶ አህመድ ጋር የተደረገው ቃለምልልስ በረቡዕ ዕትማችን ይስተናገዳል)፡፡
 
< Prev   Next >