| ወል ማርት ለሠራተኞቹ ካሳ... |
|
| Sunday, 28 September 2008 | |
|
ወል ማርት ለሠራተኞቹ ካሳ እንዲከፍል ተፈረደበት
እ.ኤ.አ በ2006 በታችኛው ፍርድ ቤት የተጀመረው ክርክር 67500 የአሁንና የቀድሞ የወል ማርት ሠራተኞችን የቡድን ጥያቄ የተመለከተ ነው፡፡ በ2ዐዐ6 ወል ማርት በከፊል ክሶቹን ማስተባበል የቻለ ቢሆንም የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኛው ቶማስ ሙርታጁ ሥልጣናቸውን ያለአግባብ ተጠቅመዋል በማለት ውሳኔውን ቀልብሷል፡፡ ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ የስር ፍርድ ቤቱ ዳኛ ሙርታጅ ከሳሾቹ ያቀረቡትን ዋነኛ ልዩ አዋቂ ምስክር የማያስተማምን ምስክር በማለት ማግለላቸውን ተችቷል፡፡ ወል ማርት ባለፈው ማክሰኞ በድጋሚ ይግባኝ ሲልም በድጋሜ ፍርዱ ፀንቷል፡፡ ዘገባው የሠራተኞቹ ጠበቃ ሮበርት ቦንሲግኖር "ክልሎች ጉዳያቸውን ራሳቸው መፈፀም አለባቸው፡፡ በይግባኝ ብዙ ጊዜ ማባከን አይኖርብንም" ማለቱን አመልክቷል፡፡ የማሳቹሴቱ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ውሳኔ ለውጥ አለማድረጉ አስተያየቱን ትክክለኛ እንደሚያደርገውም አሜሪካን ሌውዬር አስነብቧል፡፡ |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Forums |
| Contact Us |