| ኢትዮጵያን የሚያስተዋውቅ አዲስ ሲዲ ተለቀቀ |
|
| Sunday, 28 September 2008 | |
|
ይህ በ3ኛው ሺሕ ዓመት ዋዜማ የተለቀቀው ሲዲ ለቱሪስቶች፣ ለሀገር ውስጥና ለውጭ የጉዞ ወኪሎች ለመገናኛ ብዙኀን ጠቀሜታ እንደሚኖረው ይታመናል፡፡ በሲዲው ውስጥ ያለው ብሩሸር 12 ርእሰ ጉዳዮችን ከሙዚቃዊ ዳራ ጋር አካትቶ ይዟል፡፡ በመግቢያው እንደተመለከተው ቱሪስቶችም ሆኑ ሌሎች ለመጎብኘት የሚፈልጉትን አካባቢ ቅዱሳት መካናት፣ ሃይማኖታዊ ተቋማት ጥናት፣ የባህልና ዕፅዋት ብሔራዊ ፓርኮችን፣ የተፈጥሮ ደኖችን ገጽታ መረጃ ይሰጣል፡፡ ሃይማኖታዊ ንግደት (Pilgrimage) በኢትዮጵያ ሃይማኖታዊ ክብረ በዓላትን ለማንገሥ በተለያዩ አካባቢዎች ጉዞ የሚደረግባቸውን ስፍራዎች ያሳያል፡፡ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዋናነት የሚታወቁት መካኖች በሲዲው ተዘርዝረዋል፡፡ አክሱም ጽዮን፣ ደብረ ዳሞ፣ ላሊበላ፣ ግሸን ማርያም፣ የጣና ደሴቶች ገዳማት፣ ቁልቢ ገብርኤል፣ ደብረ ሊባኖስ፣ ዝቋላ አቦ፣ አዳዲ ማርያም ሲሆኑ፣ የሙስሊም ኅብረተሰቡ ዋና መካናት ነጃሽ መስጊድ፣ ሼክ ሁሴንና ሶፍ ዑመርም ተጠቅሰዋል፡፡ ከጥናትና ምርምር አኳያ ሁሉም ታሪካዊ፣ ባህላዊና ተፈጥሯዊ የቱሪዝም መስህቦች ለተመራማሪ ምሁራን ለዕውቀት መስካቸው ተጨማሪ ዕውቀት የሚያገኙበት አጋጣሚ ይፈጥርላቸዋል፡፡ ትምህርታዊ ጉዞም ያደርጋሉ፡፡ በአፋር ኤርታሌ ያለማቋረጥ የሚታየው እሳተ ገሞራ አንዱ መስህብ ነው፡፡ 83 ብሔረሰቦች የሚኖሩባት አገር ልዩ ልዩ ባህላዊ ገጽታዎችና ልምምዶች የገዳ ባህላዊ ሥልጣንና የመሳሰሉት ከጥናት መስክ ውስጥ ይካተታሉ፡፡ ሲዲው የኢትዮጵያ ሥርወ መንግሥታት አነሳስና ታሪክ፣ የአክሱም ንግሥና፣ የመካከለኛ ዘመኗን ጎንደር፣ ሐረር፣ ላሊበላ፣ ጅማ፣ የዛጉዌ አብያተ ክርስቲያናት ቅድመ አክሱም፣ ቅድመ ታሪክ-ሐዳር፣ ስለንግሥተ ሳባ፣ ስለ አዲስ አበባ መሠረታዊ ታሪኮች ተዘግቦበታል፡፡ ሲዲው ካካተታቸው ምስሎች መካከል የኢትዮጵያ ሕዝብን ልዩ ልዩ መልኮች፣ መልክዐ ምድር፣ የጢስ ዓባይ፣ የጣና፣ የሐዋሳ ሐይቅ፣ አዕዋፋት፣ የገበያ ስፍራዎች ታሪካዊ ቦታዎችና ክብረ በዓላት ይገኙበታል፡፡ |
|
| Last Updated ( Sunday, 28 September 2008 ) |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Forums |
| Contact Us |