| ኢትዮጵያ ሙስናን በመዋጋት ረገድ... |
|
| Wednesday, 01 October 2008 | |
|
ኢትዮጵያ ሙስናን በመዋጋት ረገድ መሻሻል ማሳየቷ ተመሰከረ
በጋዜጣው ሪፖርተር መቀመጫውን በርሊን ያደረገው ትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ በሙስና ረገድ ኢትዮጵያ አምና ከነበረችበት 138 ደረጃ ዘንድሮ ወደ 126ኛ መሻሻል ማሳየቷን አስታወቀ፡፡ በትራንስፓረንሲ ሪፖርት መሠረት በ126ኛ ደረጃ ከተቀመጡት ሌሎች አገራት ማለትም ኢንዶኔዥያ፣ ጉዋና፣ ሊቢያ፣ ኤርትራ እና ሞዛምቢክ ተርታ ኢትዮጵያም መግባቷን ድርጅቱ ሰሞኑን ይፋ ባደረገው የ2008 ሪፖርቱ ገልጿል፡፡ በዓለም አቀፍ ደረጃ በይበልጥ በሙስና የተዘፈቁ አገራት በሚል ድርጅቱ የጠቀሳቸው ቻድ፣ ሱዳን፣ ጊኒ እና ሶማሊያን ነው፡፡ በአንፃሩ ዝቅተኛ የሙስና ሁኔታ ይታይባቸዋል በሚል ከጠቀሳቸው አገራት መካከል ዴንማርክ፣ ስዊድን፣ ሲንጋፖር፣ ፊንላንድ፣ ስዊዘርላንድ፣ አይስላንድ፣ ኔዘርላንድ፣ አውስትራሊያና ካናዳ ይገኙበታል፡፡ |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Forums |
| Contact Us |