Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version

Tuesday
Dec 02nd
Home arrow Sections arrow ኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ...
ኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ... E-mail
Wednesday, 01 October 2008
ኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሉሙምባሺ አዲስ በረራ ይጀምራል

በጋዜጣው ሪፖርተር

ከመጪው ጥቅምት 17 ቀን ጀምሮ በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ከተማ ሉሙምባሺ አዲስ በረራ እንደሚጀምር የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለሪፖርተር ጋዜጣ በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡

በሳምንት ለአራት ቀናት በሉሙምባሺ የሚካሄደው የአውሮፕላን በረራ ከተማዋን ከዋና ዋና የእስያ፣ የአሜሪካንና የአውሮፓ ከተሞች ጋር እንድትገናኝ ያደርጋታል፡፡

በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ግዛት ሁለተኛዋ ትልቅ ከተማ የሆነችው ሉሙምባሺ የንግድ የፋብሪካ እንቅስቃሴ በስፋት የሚታይባት ስትሆን በጨርቃ ጨርቅ፣ በምግብ፣ በመጠጥና በመዳብ ምርቶችዋ ትታወቃለች፡፡

አየር መንገዱ 118 መቀመጫዎች ያሏቸው ቦይንግ 737 - 700 አውሮፕላኖችን እንደሚያሰማራ የተላከው መግለጫ ያመለክታል፡፡ በረራ የሚካሄድባቸው ቀኖች ሰኞ፣ ረቡዕ፣ አርብና ቅዳሜ ሲሆኑ መንገደኞች ለደርሶ መልስ ጉዞ 1"742 ብር እንደሚከፍሉ ተገልጿል፡፡
 
< Prev   Next >