| በአፍሪካ ሴቶች ላይ የሚደርሱ... |
|
|
| Monday, 21 January 2008 | |
|
በአፍሪካ በሴቶች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችና የመብት ገፈፋዎች በሙሉ በአህጉሪቱ የኤች.አይ.ቪ ስርጭትን ማስፋፋቱን የአፍሮል ኒውስ ዘገባ ያስረዳል፡፡ የፆታ ጥቃት ከሴቶች ተፈጥሯዊ የመጋለጥ ሁኔታ ጋር ተዳምሮ ሴቶቹ በአደጋ እንዲሆኑ ማድረጉንም ዘገባው ጠቅሷል፡፡ የኢንተር አፍሪካ ኮሚቴ ተወካይ ለንዳ ኦስርሜን የአፍሪካውያን ማህበረሰቦች ባላቸው የአመለካከት ሁኔታና አወቃቀር ምክንያት ሴቶች መብታቸው በተገፈፈበት ሁኔታ ለዓመታት ዘልቀዋል፡፡ ዘገባው በተጨማሪም የአፍሪካ ሴቶች አህጉሪቱን እያጠቃ ባለው ጦርነት ምክንያትና በሰላማዊ ሁኔታዎችም ሳይቀር በተደጋጋሚ ለአስገድዶ መደፈር ለድብደባና ለመሳሰሉ ጥቃቶች ይጋለጣሉ፡፡ ለዚህ በምሳሌነት የተጠቀሰው ደግሞ በደቡብ ሱዳን ባለው የእርስ በርስ ጦርነት ሴቶች በየዕለቱ ለሚፈፀም ጥቃት መጋለጣቸውን ነው፤ ሴቶች በዚህ አካባቢ ይደፈራሉ፣ ይገደላሉ፣ ለባርነት ታፍነው ይወሰዳሉ፡፡ ሪሰርች አክሽን ኤንድ ኢንፎርሜሽን ኔትወርክ የተባለው በአፍሪካ ሴቶች ደህንነት ላይ የሚሠራ ተቋም በበኩሉ በአፍሪካ በሴቶች በልጃገረዶች ላይ የሚደርሰው ጥቃት ተገቢው የተነፈገው መሆኑን ጠቅሰዋል ይላል ዘገባው፡፡ በተጨማሪም የአፍሪካ የተለያዩ ሀገሮች ገጠር የሚኖሩ ሴቶች ባሎቻቸው ከተሞች አካባቢ ቆይተው ሲመለሱ ኮንዶም ለመጠቀም ፈቃደኛ ባለመሆናቸው በኤች አይ ቪ እየተጠቁ ነው፡፡ በተለይ ለአስገድዶ መድፈር የሚዳረጉ ወጣት ሴቶች በተፈጥሮና የመራቢያ አካላታቸው ቫይረሱን ለመከላከል ያልዳበረ በመሆኑ ለኤች.አይ.ቪ የመጋለጥ ዕድላቸው ከፍ ያለ ነው ይላል ዘገባው፡፡ |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Forums |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Contact Us |