Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version

Tuesday
Dec 02nd
Home arrow Sections arrow የስፖርት ማዕከሉ በጥሩነሽ ዲባባ...
የስፖርት ማዕከሉ በጥሩነሽ ዲባባ... E-mail
Sunday, 05 October 2008

የስፖርት ማዕከሉ በጥሩነሽ ዲባባ ስም እንዲሰየም ተጠየቀ
በኃይሌ ሙሉ

የኦሮሚያ ክልል ለአትሌቲክስ ፌዴሬሽን በሰጠው 50 ሔክታር መሬት ላይ የሚገነባው የስፖርት አካዳሚ በጥሩነሽ ዲባባ ስም እንዲሰየም የኦሮሚያ ክልል መጠየቁን የወጣቶችና ስፖርት ሚኒስትር ወ/ሮ አስቴር ማሞ ለሪፖርተር ጋዜጣ ገለፁ፡፡

 

በቤጂንግ ኦሊምፒክ ድል ላስመዘገቡና በውድድሩ ለተሳተፉ አትሌቶች ሐሙስ ዕለት በአሰላ ስተዲየም አቀባበል በተደረገበት ወቅት ተገኝተው የነበሩት ሚኒስትሯ፣ የኦሮሚያ ክልል ቀደም ሲል የእንሰሳትና የከብት ማርቢያ የነበረውን ማዕከል የብሔራዊ አትሌቶች ማፍሪያ ይሆን ዘንድ ለአትሌቲክስ ፌዴሬሽን መስጠቱንና አካዳሚውም በአትሌት ጥሩነሽ ዲባባ ስም እንዲሰየም ጠይቋል፡፡

በአርሲ ለሚገነቧቸው የስፖርት ማዕከል መንግስት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን የጠቆሙት ወ/ሮ አስቴር፣ የማዕከሉ ግንባታ በዘንድሮው ዓመት ተጠናቅቆ በቀጣዩ ዓመት ስልጠና መስጠት እንደሚጀምር አመልክተዋል፡፡

በቀጣዮቹ ሶስት አመታትም በተለያዩ የስፖርት አይነቶች ሰልጥነው በለንደኑ ኦሊምፒክ የሚሳተፉ ተሰጥኦ ያላቸውን ወጣቶች ማፍራት እንደሚቻልም አክለው ገልፀዋል፡፡

ብቃት ያላቸው አሰልጣኞች፣ ዳኞችና ስፖርተኞች በአገሪቱ ባለመኖራቸው በስፖርቱ ዘርፍ የማስፈጸም ችግር የሚታይ መሆኑን የጠቆሙት ሚኒስትሯ ከኩባና ከቻይና ጋር በተደረገ ስምምነት መሰረት የተወሰኑ የውጭ አገር አሰልጣኞች ወደ ኢትዮጵያ መጥተው አዲስ በሚገነባው የስፖርት ማዕከልና በፌዴሬሽኖች ውስጥ የሚሰሩበት ሁኔታ መመቻቸቱን ተናግረዋል፡፡
Last Updated ( Sunday, 05 October 2008 )
 
< Prev   Next >