| በናይጄሪያ የጎምቤ አስተዳደር ... |
|
| Sunday, 05 October 2008 | |
|
በናይጄሪያ የጎምቤ አስተዳደር የገቢዎች ኮሚሽንን በስም ማጥፋት ወንጀል ከሰሰ
አስተዳዳሪው ሙሐመድ ዳንጁማ ጎሬ እና ምክትል አስተዳዳሪው ጆን ላዛረስ ዮሪዮ ኮሚሽኑን በአቡጃ በሚገኘው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የከሰሱት ኮሚሽኑ ባለፈው ሐምሌ ወር ሁለቱ ግለሰቦች በሕገወጥ መንገድ ገንዘብ ሰብስበው ለግል ጥቅም ማዋላቸውን አስመልክቶ ለተለያዩ አካላት ደብዳቤ በመፃፉ ነው፡፡ የአስተዳዳሪዎቹ ጠበቃ ጋድዛማ ኮሚሽኑን ገንዘቡን እንዲመልሱ በመጠየቅ በፃፈው ደብዳቤና ለሰብሳቢው ሂማን ቱከር 750 ሚሊዮን የናይጄሪያ ብር መጠን ያለው የካሳ ክፍያ ጠይቀዋል፡፡ ሁለቱ አስተዳዳሪዎች ኮሚሽኑ ደብዳቤውን ለሌሎች አስተዳዳሪዎች፣ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤዎች፣ እንዲሁም ለሀገሪቱ እለታዊ ጋዜጦች በማሰራጨት መጠነ ሰፊ የስም ማጥፋት ዘመቻ በማካሄድ የቀደመ ሕይወታቸውን እንዲረበሽና በህብረተሰቡ ገንብተውት የነበረውን መልካም ስምና ስብዕና መናዱን ጠቅሰዋል፡፡ ክሱ የተሰበሰበውን ገንዘብ በሕገወጥ መንገድ እንዳልተጠቀሙ ፍርድ ቤቱ ማረጋገጫ እንዲሰጣቸውና ኮሚሽኑ በግዛቷ የገንዘብ አጠቃቀም ጉዳይ ብቃት የሌለው እንደሆነም አስታውቀዋል፡፡ |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Forums |
| Contact Us |