| የዩጋንዳ መንግሥት በኮፒ ... |
|
| Sunday, 05 October 2008 | |
|
የዩጋንዳ መንግሥት በኮፒ ራይት ጥሰት ተከሰሰ
ፕሮፌሰር ካኮማ መንግሥትን በከፍተኛው ፍርድ ቤት የከሰሱት በብሄራዊ መዝሙር ስራቸው ላይ ያላቸው መብት ላይ ገደብ ተደርጎብኛል በሚል ሲሆን ለዚህም ካሳ እንዲከፈላቸው ጠይቀዋል፡፡ ካኮማ ሀገሪቱ ለ45 ዓመታት የተገለገለችበትን ብሄራዊ መዝሙር ያዘጋጁት ከፒተር ዊንጋርድ ጋር በጋራ በመሆን ነበር፡፡ የከሳሹ ጠበቃ ጆታም ቱምዌሲግዮ ፕሮፌሰር ካኮማ እ.ኤ.አ በ1963 ከአዘጋጅ ኮሚቴው የተሰጣቸው 2"000 የዩጋንዳ ብር የምስጋና መግለጫ እንጂ ከፍያቸው እንዳልሆነ ተከራክረዋል፡፡ እ.ኤ.አ በ1964 የወጣው የሀገሪቱ የኮፒ ራይት ሕግ ክፍል 4 እና 9 እ.ኤ.አ በ2006 በወጣው የኮፒ ራይትና ተዛማጅ መብቶች ሕግ ውስጥ እንዳለ የተያዘ ሲሆን ክፍሎቹ አንድ ክፍያ የተፈጸመለት ግለሰብ የአእምሯዊ መብት ጥያቄን ማንሳት እንዳይችል ይከለክላሉ፡፡ ፕሮፌሰሩ ባለፉት አርባ አምስት ዓመታት ክፍያው እንዲፈፀምላቸው ሲጠይቁ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡ ዴይሊ ሞኒተር ፕሮፌሰር ካኮማ የፒርስ አፍሪካ የሕይወት ዘመን ስኬትን ጨምሮ የበርካታ ሽልማቶች ባለቤት መሆናቸውን ዘግቧል፡፡ |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Forums |
| Contact Us |