Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version

Tuesday
Dec 02nd
Home arrow Sections arrow የማረሚያ ቤቶች ስፖርት ክለብ...
የማረሚያ ቤቶች ስፖርት ክለብ... E-mail
Wednesday, 08 October 2008

የማረሚያ ቤቶች ስፖርት ክለብ በገንዘብ እጥረት ችግር ገጥሞታል

የበርካታ ጀግና አትሌቶች መገኛ የሆነው ፌዴራል ማረሚያ ቤቶች ስፖርት ክለብ የፋይናንስ እገዛ ካልተደረገለት ቀጣይነቱ አደጋ ላይ እንዳይወድቅ ከስፖርት ክለቡ የተገኘው ዜና አመለከተ፡፡

 

ከሳምንታት በፊት ለቤጂንግ ኦሊምፒክ ጀግኖች የማዕረግና የማበረታቻ ሽልማት በግዮን ሆቴል ያበረከተው ፌዴራል ማረሚያ ቤት ስፖርት ክለብ የስፖርት ክለቡ በአሁኑ ሰዓት የገንዘብ እጥረት የክለቡን ሕልውና ክፉኛ እየተፈታተነው በመሆኑ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች አስፈላጊውን እገዛ በማድረግ ሊታደጉት እንደሚገባ ኃላፊዎቹ አመልክተዋል፡፡

በግዮን ሆቴል የማዕረግና የማበረታቻ ሽልማት በተሰጠበት እለት የስፖርት ክለቡ በተለይ በአትሌቲክስ ተተኪዎችን ለማፍራት ቀርቶ፣ ያሉትን አትሌቶች እንኳ መጓጓዥና የላብ መተኪያ አሟልቶ ማቅረብ እየተሳነው እንደሚገኝ የክለቡ የበላይ ጠባቂ የሆኑት የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ማዕረጉ ሀብተ ማርያም የተናገሩትን በመጥቀስ በአሁኑ ሰዓት በክለቡ የተጋረጠውን የገንዘብ እጥረት የገለፁት የክለቡ ኃላፊዎች አፋጣኝ የገንዘብ ድጋፍ እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል፡፡

በተለያዩ የዓለምና የኦሊምፒክ አደባባይ የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ከፍ ብሎ እንዲውለበለብ ካደረጉ ብርቅዬ አትሌቶች አትሌት ደራርቱ ቱሉ፣ ፋጡማ ሮማ፣ ጥሩነሽ ዲባባና ስለሺ ስህን የማረሚያ ቤቶች ስፖርት ክለብ ያፈራቸው መሆኑን ያመለከተው ዜና "ክለቡን ማዳን የሁሉም ዜጋ ነው" ሲሉ ኃላፊዎቹ በተለይ ለሪፖርተር ጋዜጣ ገልፀዋል፡፡
 
< Prev   Next >