Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version

Tuesday
Dec 02nd
Home arrow Sections arrow "እያደር የሚጣፍጠው ወይን"...
"እያደር የሚጣፍጠው ወይን"... E-mail
Wednesday, 08 October 2008

Image"እያደር የሚጣፍጠው ወይን" 1 ሚሊዮን ጉርሻ ይጠብቀዋል
በሔኖክ ያሬድ

መስከረም 18 ቀን 2001 ዓ.ም በራሱ ተይዞ የነበረውን የዓለም ማራቶን ክብረ ወሰን በጀርመኗ በርሊን ከተማ በ27 ሰከንድ የሰበረው ኃይሌ ገብረሥላሴ በቅርቡ በዱባይ ማራቶን ካሸነፈ 1 ሚሊዮን ዶላር እንደሚሸለም አዘጋጅ ክፍሉ ገለፀ፡

 

ኃይሌ በርሊን ላይ በ2 ሰዓት 03 ደቂቃ 59 ሰከንድ በመግባት ማሸነፉንና ክብረ ወሰን መጨበጡን በአድናቆት ከዘገቡት መገናኛ ብዙሃን መካከል "የፍራንስ 24" ዘገባ የኃይሌን ገድል ስኬታማነት ከቆየ ወይን ጋር አነጻጽሮታል፡፡ "እያደር የሚጣፍጠው ወይን" በማለት፡፡ የ35 ዓመቱ ኃይሌ ዕድሜው ለሩጫ ቢገፋም ጣፋጭ ድልን እያጣጣመ መሆኑን አመልክቷል፡፡

የኃይሌ አዲሱ 26ኛው ክብረ ወሰን በታሪክ ከ2ሰዓት 04 ደቂቃ በታች የገባ የመጀመሪያው ሰው አድርጎታል፡፡ ከአንድ ዓመት በፊት ኃይሌ በፖል ቴርጋት በ2 ሰዓት 04 ደቂቃ 55 ሰከንድ ተይዞ የነበረውንና ቴርጋት ከ2 ሰዓት 05 ደቂቃ በታች የገባ የመጀመሪያው አትሌት የተባለበትን ክብረ ወሰን፣ በ2ሰዓት 04 ደቂቃ 24 ሰከንድ በመፈጸም ክብሩን መጨበጡ ይታወሳል፡፡ ኃይሌ የበርሊን ማራቶንን ሦስት ጊዜ በማሸነፉም የመጀመሪያው ሰው ሆኗል፡፡

የማራቶንን ክብረ ወሰን ለመጀመሪያ ጊዜ የሰበረው ኢትዮጵያዊ አበበ ቢቂላ ሲሆን፣ በ1957 ዓ.ም በቶኪዮ ኦሊምፒክ 2ሰዓት 12ደቂቃ በመፈፀም የዓለምና የኦሊምፒክ ክብረ ወሰን በመስበር የክብረ ወሰን ፋና ወጊ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ሁለተኛው ክብረ ወሰን በ1980 ዓ.ም ሮተርዳም (ሆላንድ) በ2 ሰዓት 06 ደቂቃ በመግባት ሰዓቱ በመስበር ያሸነፈው በላይነህ ዴንሳሞም ይታወሳል፡፡
Last Updated ( Thursday, 09 October 2008 )
 
< Prev   Next >