| የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦትን 50... |
|
| Sunday, 12 October 2008 | |
|
የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦትን 50 ከመቶ ከፍ ለማድረግ ታቅዷል
የአካባቢ ተቆርቋሪዎች መድረክ ታዳሽ ኃይሎችን አስመልክቶ መስከረም 30 ቀን 2001 ባካሄደው የግማሽ ቀን አውደ ጥናት ላይ የቀረበው ይኸው ጥናት እንዳመለከተው የትራንስፖርት መሰረተ ልማት መስፋፋት እያደገ መምጣቱ የሚያበረታታ ቢሆንም ከነዳጅ ፍላጎት ጋር መጣጣም ይኖርበታል፡፡ ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት እውን መሆን ኢነርጂን በብዛትና በጥራት የማቅረቡ ጉዳይ በእጅጉ ወሳኝ መሆኑን ጥናቱ አመልክቶ ከሀገሪቱ ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር ሲታይ ግን አብዛኛው ሕዝብ ባለው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮች ሳቢያ የኤሌክትሪክ አቅርቦትን በጥራትና በብዛት እንደማያገኝ አስረድቷል፡፡ ኢትዮጵያ ኃይድሮ፣ ባዮማስ ወይም ባዮፊዩል፣ ሶላር፣ ነፋስና ጂኦተርማል የመሳሰሉ ታዳሽ ኃይሎች በብዛት እንዳሏት፣ ነገር ግን በፋይናንስ እና በተቋም ውስንነት የተነሳ በሚገባ እንዳልተጠቀመችባቸው አመልክቷል፡፡ በአክሱም ሆቴል አዳራሽ በተካሄደው በዚሁ አውደ ጥናት ላይ በሀገሪቱ የሚገኙትን ታዳሽ ኃይሎች ጥቅም ላይ ለማዋልና በሕብረተሰቡም ዘንድ በብዛት እንዲታወቁ ለማድረግ የሚያስችሉ ጠቃሚ ሀሳቦች የተሰነዘሩ ሲሆን ውይይትም ተካሄዷል፡፡ |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Forums |
| Contact Us |