Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version

Tuesday
Dec 02nd
Home arrow Sections arrow የግብጽ ፕሬዚዳንት ዋና አዘጋጁን...
የግብጽ ፕሬዚዳንት ዋና አዘጋጁን... E-mail
Sunday, 12 October 2008

Imageየግብጽ ፕሬዚዳንት ዋና አዘጋጁን ይቅርታ አደረጉለት

የግብጽ ፕሬዚዳንት ሆስኒ ሙባረክ ስለ ጤናቸው ወቅታዊ ሁኔታ የፃፈው ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ተፈርዶበት እስር ቤት የነበረ ቢሆንም ይቅርታ አድርገውለት መፈታቱን ቢቢሲ ዘገበ፡፡

 

የአል-ዱከቱር ጋዜጣ ዋና አዘጋጅና የፕሬዚዳንቱ ዋነኛ ተች የሆነው ዋና አዘጋጁ ኢብራሒም ኢሳ ባለፈው ወር የሁለት ወራት እስራት የተፈረደበት በጋዜጣው ላይ የወጣው ጽሁፍ በፍርድ ቤቱ እይታ የህዝብ ደህንነትን የሚያውክ ሆኖ በመገኘቱ ነው፡፡

በአገሪቱ የመንግሥት መገናኛ ብዙሃን ፕሬዚዳንቱ በታጠቁ ሃይሎች ቀን ይቅርታ ያደረጉለት ለሃሳብ ነፃነት ትኩረት እንደሚሰጡ ለማረጋገጥ መሆኑን ተገልጿል፡፡ የ80 ዓመቱ ፕሬዚዳንት በእሳቸውና በማንኛውም የግብጽ ዜጋ መካከል ዘላቂ አለመግባባት እንዲፈጠር እንደማይፈልጉም ይፋ አድርገዋል፡፡

የቡሽ አስተዳደር ቃል አቀባይ ባለፈው ዓመት ዋይት ሃውሰ በግብጽ ዋና አዘጋጆች ላይ እየደረሰ ያለው ስቃይና እንግልት እንደሚያሳስባት ገልፀው ነበር፡፡
Last Updated ( Monday, 13 October 2008 )
 
< Prev   Next >