|
Sunday, 27 January 2008 |
|
ሠላም ሪፖርተሮች፡፡ በረቡዕ ጥር 14 ቀን 2ዐዐዐ ዓ.ም. ዕትማችሁ ላይ "የአዲስ አበባ ዋና ሥራ አስኪያጆች ሊዘዋወሩ ነው" የሚል ዜና አስነበባችሁን፡፡
በመጀመሪያ እናንተን ላርምና ወደ ሌላው ልግባ፡፡ አዲስ አበባ ያላት ዋና ሥራ አስኪያጅ አንድ ነው፡፡ ስለዚህ የአዲስ አበባ ከማለት ይልቅ የክፍለ ከተሞች ሥራ አስኪያጆች ብትሉት የተሻለ ነበር፡፡ ለመሆኑ በአስተዳደሩ ስር ያሉትን ክፍለ ከተሞች ሥራ አስኪያጆች አንዳቸውን ከሌላቸው የሚያለያያቸው አሰራር አለ? የለም፡፡ ምናልባት የየካው ወደ ጉለሌ ቢቀየር አብረውት የሚሰሩትን ሰዎች ስምና ባህሪ እስከሚያጠና አንድ ሳምንት የተሻለ ሊሰራ ይችላል፡፡ ግን ወዲያው ወደ ተለመደ አሠራሩ ይገባል፡፡ ስለዚህ ሙሉ በሙሉ ከሥልጣን አስወግዶ ሌላ መተካት ካልተቻለ (አዲሱም እስከ ሚለምድ) ጉልቻ ቢለዋወጥ ወጥ አያጣፍጥም እንዲሉ ነው ቢታሰብበት ጥሩ ነው እላለሁ፡፡ (ፋሲካ ይግዛው፣ ከቂርቆስ) |