|
Sunday, 27 January 2008 |
|
በረቡዕ ጥር 14 ሪፖርተር ጋዜጣ የወጣው የአዲስ አበባው መናፈሻ ጉዳይ የሚያናድድ ነው፡፡
የህዝብ ንብረት የሆነ መናፈሻን እንደ ንግድ ተቋም አንዴ በውክልና፣ አንዴ በአስተዳደር አካል ሌላ ጊዜ በመንግሥት እጅ ወደ ላይ ወደ ታች ቢልም ለሁለት ዓመታት ያህል እንደወታደራዊ ቀጠና ከቤተ መንግሥት እኩል "እለፍ" የሚባልበት ህዝብም አይደለም ገብቶ ዘና ሊልበት የሚያልፈው እንኳን በዳር በዳር በቀስታ እርምጃ ነው፡፡ ለማሳመር በተሰጠ ውል ችግር መፈጠሩ እየተናገረ ይገኛል፡፡ የሆነ ሆኖ ውል መስጠትና ቦታው ከአገልግሎት መስጫነት ለረጅም ጊዜ እንድገለል ለምን አስፈለገ? የውሉ ዝርዝር ነገሮችስ በእውነት የህዝብ ንብረት አጠቃቀምን መሰረት ያደረጉ ናቸው? መልኩ ምንም ይሁን ምንም ተጨማሪ ውበት ይቅርብንና መናፈሻው በአስቸኳይ ለባለቤቱ ለህዝብ ክፍት ይሁን፡፡ (ሙከመር፣ ከወሎ ) |