| የአንበጣ መንጋን ለመከላከል... |
|
| Sunday, 27 January 2008 | |
|
የአንበጣ መንጋን ለመከላከል እንቅስቃሴ በመደረግ ላይ ነው በኢትዮጵያ ውስጥ በተለያዩ ሦስት ክልሎች በሚገኙ ልዩ ልዩ ሥፍራዎች የተከሰተውን የበረሃና ተዛማጅ የአፍሪካ አንበጣ መንጋ ለመከላከል የሚያስችል አንቅስቃሴ በመከናወን ላይ መሆኑን የእንስሳትና እፅዋት ጤናና ጥራት ኢንስፔክሽንና ቁጥጥር መምሪያ አስታወቀ፡፡ የአንበጣው መንጋ የተከሰተው በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች፣ በኦሮሚያና በጋምቤላ ክልሎች በሚገኙ ልዩ ልዩ ሥፍራዎች መሆኑንም በመምሪያው የሰብል ጥበቃ ባለሙያ ወይዘሮ አዜብ ለማ ገልፀዋል፡፡ በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል በልዩ ልዩ ሥፍራዎች እንዲሁም በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሐረርጌ ዞን የተከሰተው የበረሃ አንበጣ መንጋ ሲሆን፣ ተዛማጅ የአፍሪካ አንበጣ የታየው ደግሞ በጋምቤላ ክልል መሆኑን አስረድተዋል፡፡ በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል በኮንሶ ወረዳና በአካባቢው የታየውን የበረሃ አንበጣ መንጋ ለማጥፋት ከጥር 13 እስከ ጥር 15 ቀን 2ዐዐዐ ድረስ በተካሄደው እንቅስቃሴ 1065 ሊትር ኬሚካል መረጨቱንና በዚህም 1015 ሔከታር መሬት ከአንበጣ መንጋ ነፃ ለማድረግ መቻሉን ባለሙያዋ ተናግረዋል፡፡ በቀሩት ሥፍራዎች የተከሰተውን የአንበጣ መንጋ ሁኔታ ለማየትና የመድኃኒት መርጨቱንም ሥራ ለማከናወን የሚያስችል አንድ የባለሙያዎች ቡድን ከጥር 15 ቀን 2000 ጀምሮ ወደ ተጠቀሱት ሥፍራዎች መንቀሳቀሱን አስታውቀዋል፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ዝርዝር ማብራሪያ ለማግኘት ለመምሪያው ምክትል አስተባባሪ በፀሃፊዎቻቸው በኩል መልዕክት ብናስተላልፍም ሊሳካልን አልቻለም፡፡ |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Forums |
| Contact Us |