| ኬንያውያን ሴቶች ጆንያ እንዲለብሱ ተጠየቁ |
|
|
| Sunday, 27 January 2008 | |
|
ኬንያውያን ሴቶች በሀገራቸው ያለው ብጥብጥ እስኪቆም ድረስ ጆንያ እንዲለብሱ ጥሪ ቀረበ፡፡ ቢቢሲ እንደዘገበው በሁለት ሴቶች አነሳሽነት የተጀመረው ይህ ተግባር እየተካሄደ ያለውን ሁከት መቃወሙን ለማሳየትና ለሀገሪቱና ለሟቾቹ ሀዘንን ለመግለፅ የሚል ዓላማ ያለው ነው፡፡ ከዚህ ሌላ ለቢቢሲ ድምፃቸውን ያሰሙት አነሳሾችና ጓደኞቻቸው ፍትህ እንዲሰፍን ለመጠየቅም ጭምር ድርጊቱን እየፈፀሙ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ "በኬንያ ሰላም እስኪሰፍን ድረስ እንዲህ መልበሴን እቀጥላለሁ ሌሎችም እንዲከተሉን እጠይቃለሁ፡፡ ይህ ነገር ለውጥ እስኪመጣ ይቀጥላል" ብላለች አስተባባሪዋ ለቢቢሲ፡፡ በተጨማሪም "እስከዛሬ እየታገልን ያለነው ሕገመንግሥቱ እንዲለወጥና ሥልጣን ከተወሰኑ ሰዎች እጅ እንዲወጣ ነው፡፡ ይህ ከሆነ ነፃ የሆነ የፍትህ ሥርዓት ይኖረናልም" ብላለች፡፡ እንደ አስተባባሪዋ ጆንያ ለብሶ በመዘዋወር ተቃውሞን መግለፅ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ ከማድረግ ይሻላል፡፡ በአምላክና በሕዝቡ ፊትም ራስን ዝቅ አድርጎ ማቅረብን ያሳያል፡፡ ከዚህ ሌላ ኬንያውያን ሴቶች መሪዎችና ሕዝቡ ሁሉ ሰከን ባለመንፈስ እንዲወያዩ ለማድረግና የተፈጠረውን የጎሰኝነት መንፈስ እንዳይንሰራፍ ለማድረግ በተቃውሞው እንዲተባበሩ በአስተባባሪዎቹ ተጠይቀዋል፡፡ |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Forums |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Contact Us |