Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version

Tuesday
Dec 02nd
Home arrow Sections arrow የምርጫ ቦርድ ሊቀመንበር የመኪና አደጋ ...
የምርጫ ቦርድ ሊቀመንበር የመኪና አደጋ ... E-mail
Sunday, 03 February 2008
የምርጫ ቦርድ ሊቀመንበር የመኪና አደጋ ደረሰባቸ
በአደጋው አንድ ሰው ሞቷል

የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሊቀመንበር ዶክተር መርጊያ በቃና ባጋጠማቸው የመኪና ግጭት በህይወትና በንብረት ላይ ጉዳይ ደረሰ፡፡ የዶክተሩ ሾፌር በዋስ ተለቀዋል፡፡
ዶክተር መርጊያ የመኪና ግጭት ያጋጠማቸው ከአዲስ አበባ ወደ ደብረዘይት በሚወስደው መንገድ በአቃቂና ዱከም ከተሞች መካከል ገላን ከተማ ነው፡፡

የአይን እማኞች እንደገለፁት ገላን ከተማ አምባሳደር ልብስ ስፌት ፋብሪካ አጠገብ የመኪና አደጋው የደረሰው ጥር 22 ቀን 2000 ዓ.ም ከምሽቱ 4 ሰዓት አካባቢ እንደሆነ የገላን ፖሊስ ለሪፖርተር ገልጿል፡፡

ዶክተር መርጊያ የነበሩባት መኪና (ዲስከቨሪ) የተጋጨችው ከዲኤክስ መኪና ጋር ሲሆን የዲኤክስ ሾፌሩ ህይወታቸው ማለፉ ታውቋል፡፡ የገላን ፖሊስ ስለ አደጋው በዝርዝር ባይገልጽም የዲኤክሷ አሽከርካሪ ብቻቸውን እንደነበሩና ህይወታቸው እንዳለፈ ገልጿል፡፡ ዶ/ር መርጊያ ወደ ሆስፒታል እንደተወሰዱ አስታውቋል፡፡

የዶክተር መርጊያ ሾፌር ከአደጋው በኋላ በቁጥጥር ሥር ውለው አቃቂ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቀርበው በዋስ እንደተለቀቁ ለመረዳት ተችሏል፡፡  

በአሰግድ ተፈራ
Last Updated ( Sunday, 03 February 2008 )
 
< Prev   Next >