Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version

Monday
Oct 13th
Home arrow Sections arrow የኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ...
የኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ... E-mail
Sunday, 06 January 2008

የኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ ከ93 ሚሊዮን ብር በላይ የተከፈለ ካፒታል አሰባሰበ

በተያዘው የበጀት ዓመት ሥራ ይጀምራሉ ተብለው የአክስዮን ሽያጭ በማከናወንና መመስረታቸውን ይፋ ካደረጉት የግል ባንኮች መካከል አንዱ የሆነው የኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ የተፈረመ ካፒታልና የተከፈለ 93 ሚሊዮን ብር ማሰባሰቡን አስታወቀ፡፡


በሂልተን ሆቴል ታህሣሥ 19 ቀን 2000 በተካሄደው የባለአክስዮኖች ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ባንኩን በቦርድ አባልነት የሚመሩ አባላት ተመርጠዋል፡፡

በኦሮሚያ የቢዝነስ እንቅስቃሴ አለባቸው ተብለው በታመነባቸው ገጠራማ ወረዳዎች ቅርንጫፎችን በመክፈት ሥራ እንደሚጀምር ያስታወቀው ይህ ባንክ እስካሁን ድረስ ከ4 ሺህ በላይ የሚሆኑ ግለሰቦችና ድርጅቶች አክሲዮን ገዝተዋል፡፡

በኢትዮጵያ ባንክ ለማቋቋም በብሄራዊ ባንክ በኩል በተደረገው ህግ መሰረት ሥራ ለመጀመር ባንኩ የተከፈለ 100 ሚሊዮን ብር እንዲኖረው የሚያስገድድ በመሆኑ የኦሮሚያ ባንክ ይህንን በማሟላትና የተመረጡትን የቦርድ አባላት በማጽደቅ ወደ ሥራ የሚገባ መሆኑንም ለማወቅ ተችሏል፡፡

ከዚህ ባንክ ሌላ አምራች የሚሆኑ የግል ባንኮች በአክሲዮን ሽያጭ ላይ የሚገኙ ሲሆን አክሰስ ባንክ በሚል መጠሪያ የተቋቋመው የግል ባንክ ለመቋቋም የሚያስፈልገውን መስፈርት ካሟላ በኋላ ስያሜውን እንዲቀይር በብሔራዊ ባንክ በመገደዱ አክሰስ የሚለውን ዘመን ባንክ በሚል መጠሪያ ቀይሮ ሥራው ይጀምራል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

አክሰስ ባንክ ስያሜውን እንዲቀይር የተገደደው በናይጄሪያ ተመሣሣይ ስም ያለው ባንክ አለ በሚል ነው፡፡

አሁን በመቋቋም ላይ ያሉትን ጨምሮ ባሳለፍናቸው 12 ዓመታት ከተቋቋሙት የግል ባንኮች ጋር ሲደመር በአገሪቱ ውስጥ ያሉትን የግል ባንኮች ቁጥር አስራ ሁለት ያደርሰዋል፡፡

በዳዊት ታዬ

 
< Prev   Next >