Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Sunday
Jul 06th
Home arrow Sections arrow ከወርቅ ማጭበርበር በተያያዘ...
ከወርቅ ማጭበርበር በተያያዘ... Print E-mail
Sunday, 10 February 2008
ከወርቅ ማጭበርበር በተያያዘ ተጠርጥረው የታሰሩት ተሸለሙ

በብሄራዊ ባንክ በተፈፀመ የወርቅ ማጭበርበር ጋር በተያያዘ ተጠርጥረው የታሰሩት የኑር ህንፃ ባለቤት አቶ ኑረዲን መሀመድ ከፍተኛ ግብር ከፋይ ተብለው ተሸለሙ፡፡
በተሰማሩበት የአከራይ ዘርፍ ከፍተኛ ግብር ከፋይ ተብለው ጥር 27 ቀን 2000 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር የምስክር ወረቀት የተሰጣቸው አቶ ኑረዲን በአዲስ አበባ መስተዳድር ከልደታ ክ/ከተማ ግብር ከፋዮች ውስጥ ከ1997 እስከ 1999 ባሳዩት የገቢ ማሳወቂያ ወቅት፣ በተሰማሩበት የንግድ ዘርፍ ከፍተኛ ግብር ከከፈሉት መካከል በ5ኛ ደረጃ አግኝተዋል፡፡ መስተዳድሩ ለተጠርጣሪው ግለሰብ በሰጠው የምስክር ወረቀት ባለሀብቱ በገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 286/94 መሰረት ለሌሎች አርአያ ሆነው እንዲቀጥሉ ጠይቋል፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ በተከናወነው የሽልማት ዝግጅት ከየክፍለ ከተማው ከፍተኛ ግብር ለከፈሉ ግብር ከፋዮችና በ2000 በጀት ዓመት በመጀመሪያው 6 ወራት በገቢ ዕቅድ አፈፃፀማቸው የተሻለ ክንውን ላላቸው ክ/ከተሞች ሽልማት ተሰጥቷል፡፡ በእለቱ በቦታው ተገኝተው ሽልማቱን የሰጡት ከንቲባ ብርሃነ ደሬሳ ናቸው፡፡

ከወርቅ ማጭበርበር ጋር በተያያዘ ተጠርጥረው ጥር 5 ቀን 2000 ዓ.ም በፖሊስ ቁጥጥር ሥር የዋሉት አቶ ኑረዲን ሽልማቱን በአካል ተገኝተው ለመውሰድ ባለመቻላቸው እርሳቸውን ወክለው ባለቤታቸው ተቀብለውላቸዋል፡፡

በብሄራዊ ባንክ ከተፈጸመ የወርቅ ማጭበርበር ጋር በተያያዘ በርካታ ሰዎች ተጠርጥረው መታሰራቸውን መዘገባችን የሚታወስ ነው፡፡ ከነዚህም መካከል በወርቅ ኤክስፖርት ስራ ተሰማርተው የሁለተኛ ደረጃ በማግኘት በውጪ ንግድ ቀን ከጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ እጅ ሽልማት የተቀበሉት ይገኙበታል፡፡

በኃይሌ ሙሉ
 
< Prev   Next >