| በማዶና የገቢ ማሰባሰቢያ... |
|
|
| Sunday, 10 February 2008 | |
በማዶና የገቢ ማሰባሰቢያ ዝነኛ ተዋናዮች ተገኙበማላዊ የሚገኙ ህፃናትንና ዩኒሴፍን ለመርዳት ማዶና በኒውዮርክ ባዘጋጀችው ማሰባሰቢያ ዝነኛና ታዋቂ ግለሰቦችና ተዋናዮች መገኘታቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡ ቶም ክሩዝ፣ ጄኒፈር ሎፔዝ እና ግዊንች ፓልትሮው በሥነ ስርዓቱ ላይ ከተገኙ በርካታ ኮከብ አርቲስቶች መሃል ነበሩ፡፡ ከዝግጅቱ 3.7 ሚሊዮን ዶላር ገቢ የተገኘ ሲሆን፣ ዩኒሴፍ በማላዊ ለሚገኙ ህፃናት ለሚያከናውናቸው የበጐ አድራጐት ሥራዎች ይውላል፡፡ ማዶናና ባለቤቷ ሬይ ሪቺ ከማላዊ ወንድ ህፃን በማደጐ ለማሳደግ በሂደት ላይ ናቸው፡፡ “ታዋቂ ሰዎች እንደ በጐ አድራጊ ድርጅቶች እንዲሆኑ እፈልጋለሁ፡፡ እነሱ የገንዘብ ቼክ እንዲፅፉልኝ ብቻ አልፈልግም፡፡ የምፈልገው ልባቸውን በጥቂቱ እንዲሰጡኝ ነው” በማለት በዝግጅቱ ላይ ተናግራለች፡፡ በኮሜድያን ክሪስ ሮክ የተዘጋጀው አንድ ሰሃን እራት የ2500 ዶላር ግልፅ ጨረታ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ ባን ኪሞን ጨምሮ የድርጅቱን ባለስልጣናት ያዝናና ነበር፡፡ |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Forums |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Contact Us |