| በኢትዮጵያ የሚገኙ 27 ከፍተኛ... |
|
|
| Wednesday, 13 February 2008 | |
|
በኢትዮጵያ የሚገኙ 27 ከፍተኛ የቡና ቀማሾች የሕ (የኳሊቲ) ደረጃ ፈቃድ አገኙ
ኢትዮጵያ በአለም ደረጃ የኪው"ኳሊቲ) ደረጃ የቡና ጥራት መርማሪዎችን አሰልጥና አስመረቀች፡፡ አሜሪካ የሚገኘው ኮፊ ኳሊቲ ኢንስቲትዩት፣ ቡት ኮፊ ኮንሰልቲንግ እና ዩ ኤስ አይድ ሲንትራክ ከቡና ጥራትና መቆጣጠር ማዕከል ጋር በመተባበር በሰጡት ስልጠና ባለፉት ሶስት ወራት ጊዜያት ውስጥ 27 ከፍተኛ የቡና ቀማሾች የኪው (ኳሊቲ) ደረጃ ፈቃድ አግኝተዋል፡፡ የቡት ኮፊ ኮንሰልቲንግ ኤንድ ትሬኒንግ አማካሪ አቶ ዳንኤል ሙሉ ለሪፖርተር ጋዜጣ እንደገለፁት ከፍተኛ የቡና ቀማሾቹ የኪው (ኳሊቲ) ደረጃ ፈቃድ ማግኘታቸው ኢትዮጵያ ጥራት ያለው ቡና በብዛት ወደ ውጭ እንድትልክ ያስችላታል፡፡ እንደ አቶ ዳንኤል ገለፃ ስልጠናቸውን አጠናቅቀው ባለፈው ሳምንት የተመረቁት ኢትዮጵያውያኖች የቡና ጥራት መርማሪዎች የኪው ደረጃ ፈቃዳቸውን ከማግኘታቸው በፊት ለ23 ቀናት ተከታታይ ፈተና ተሰጥቷቸዋል፡፡ በአሁኑ ሰዓት በዓለም ላይ የኪው (ኳሊቲ) ደረጃ ፈቃድ ያላቸው የቡና ቀማሾች 315 ብቻ ናቸው፡፡ ኮሎምቢያ 89፣ ጃፓን 54፣ ኤልሳልቫዶር 33፣ ኮስታሪካ ደግሞ 27 የኪው ደረጃ የቡና ቀማሾች አሏቸው፡፡ ባለፈው ህዳር ወር 12 የቡና ቀማሾችን አሁን ደግሞ 15 የቡና ቀማሾችን ያስመረቀችው ኢትዮጵያ በአለም ደረጃ ከኮስታሪካ ጋር በ4ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች፡፡ በኃይሌ ሙሉ |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Forums |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Contact Us |