Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Sunday
Jul 06th
Home arrow Sections arrow ታዳጊ ሕፃን የደፈረው በዋስ በመለቀቁ...
ታዳጊ ሕፃን የደፈረው በዋስ በመለቀቁ... Print E-mail
Wednesday, 13 February 2008
ታዳጊ ሕፃን የደፈረው በዋስ በመለቀቁ ነዋሪዎችና የሴቶች ጉዳይ ተቃወሙ

በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልላዊ መንግሥት በአሶሳ ከተማ ቀበሌ 04 ውስጥ የ13 ዓመት ታዳጊ ሕፃን በመድፈር ተጠርጥሮ የታሰረው ግለሰብ በ500 ብር ዋስ በመለቀቁ የክልሉ ሴቶች ጉዳይ ጽ/ቤትና የከተማው ነዋሪዎች ተቃውሟቸውን ለክልሉ መንግሥትና ፍርድ ቤቶች ማሰማታቸውን ለሪፖርተር ጋዜጣ ገለፁ፡፡
የሕፃኗ አመልሄር ሸሪፍ አባት እንደገለፁት እናት የስኳር ሕመምተኛ በመሆናቸው ወደ አዲስ አበባ ለሕክምና በመጡበት ወቅት ተጠርጣሪው ብቸኝነቷን አውቆ፣ ከቁራን ትምህርት ቤት ስትመለስ ዝናብ ይዘንብ ስለነበር "እንድትጠለል ጠይቋት ወደ ቤቱ ካስገባት በኋላ እንደደፈራት ምስክሮች ለፍርድ ቤት መናገራቸውንና በሐኪም መረጋገጡን ወላጅ አባቷ ተናግረዋል፡፡

የክልሉ ወረዳ ፍርድ ቤት ግለሰቡ ሕፃኗን መድፈሩን የሚያረጋግጡ የሕኪምና የሰው ማስረጃዎች እያሉ፣ "በቂ ማስረጃ አላገኘሁም" በማለት ተጠርጣሪውን መልቀቁ አግባብ አለመሆኑን የወረዳው ሴቶች ጉዳይ ኤክስፐርት ወ/ሮ ዘነበች አለምነህ ገልፀዋል፡፡

የወረዳው ፍርድ ቤት መዝገቡን መዝጋቱ አግባብ አይደለም ብለው በማመናቸው የክልሉ ፍትህ ቢሮና የዞን ፍትህ፣ እንደገና ማየት ስለሚችሉ፣ የውሳኔው ግልባጭ እንዲሰጥ ቢጠየቅ ተግባራዊ ለማድረግ ፈቃደኛ አለመሆኑን ወ/ሮ ዘነበች ተናግረዋል፡፡ ይሁንና የወረዳው ሴቶች ጉዳይ ቢሮና ነዋሪው ባሰማው የተቃውሞ ድምጽ ወደ ዞን ፍርድ ቤት እንዲሄድ ማድረጋቸውን ኤክስፐርቷ ተናግረዋል፡፡

በአሁኑ ጊዜ ኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ዜጎችን እየፈጀ ባለበት ወቅት ህፃናትን በማታለልና በማስገደድ የመድፈር ወንጀል የሚፈጽሙ ግለሰቦችን ዓለም እያወገዘና የማያዳግም እርምጃ እየወሰደ ባለበት ሰዓት፣ ሙሉ ማስረጃ የቀረበበትን ተጠርጣሪ በዋስና በነፃ ማሰናበት የአገሪቱ የሕግ ጉዳይ ሊፈተሽና ሊታይ የሚገባው መሆኑን ወ/ሮ ዘነቡ አስረድተዋል፡፡

ጉዳዩ ወደ ሴቶች ቢሮና ኅብረተሰቡ የደረሰው ለወረዳው ፍ/ቤት ተደፋሪዋ ሕፃን አመልሄር ጥር 26 ቀን 2000 ዓ.ም ፍርድ ቤቱ ተጠርጣሪውን በ500 ብር ዋስ እንዲለቀቅ የወሰነውን በመቃወም የፃፈችው ደብዳቤ ምላሽ ባለማግኘቱ፣ ወላጅ አባቷ ባሰሙት አቤቱታ መሆኑን ነዋሪዎቹ ገልፀዋል፡፡

በታምሩ ጽጌ
 
< Prev   Next >