Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Sunday
Jul 20th
Home arrow Sections arrow የውጭ ምንዛሬ ችግርን ለማቃለል...
የውጭ ምንዛሬ ችግርን ለማቃለል... Print E-mail
Wednesday, 13 February 2008
Image
የዓለም ባንክ ፕሬዚዳንት ሮበርት ዞሊክ
የውጭ ምንዛሬ ችግርን ለማቃለል የዓለም ባንክ ቦርድ እንደሚወያይ ተጠቆመ


ኢትዮጵያ ያለባትን የውጭ ምንዛሬ ችግር ለማቃለል የዓለም ባንክ አዲስ የእገዛ እስትራቴጂ ለማውጣት ከቦርዱ ጋር እንደሚነጋገር ገለፀ፡፡ ከሁለት ወራት በኋላ መፍትሄ እንደሚያገኝም የዓለም ባንክ ፕሬዚዳንት ሮበርት ዞሊክ ገልፀዋል፡፡
ፕሬዚዳንቱ በአዲስ አበባ በተካሄደው የአፍሪካ ሕብረት 10ኛው መደበኛ ስብሰባ ላይ በተሳተፉበት ወቅተ በሰጡት ቃለ መጠይቅ ኢትዮጵያ ሁሉን አቀፍ የሆነ እድገት  እያስመዘገበች መሆኗን ገልፀው ይህን ለማጠናከር አዲስ የእገዛ ስትራቴጂ ለማውጣት ከዓለም ባንክ ቦርድ ጋር እንደሚነጋገሩ በሁለት ወራት ውስጥ መልስ እንደሚያገኝም ጠቁመዋል፡፡

አገሮች የሚያሳዩት ብቃት ከዓለም የልማት ማህበር ፕሮግራም የተለየ ብድርና እርዳታ እንደሚያገኙ ገልፀው ኢትዮጵያ እያሳየች ባለው ጥሩ ብቃት ከመቶ ሚሊዮን ዶላር በላይ እገዛ በእርዳታ ወይም በአነስተኛ ወለድ የሚታሰብ ብድር እንደሚሰጣትም ተናግረዋል፡፡

ኢትዮጵያ የዓለም ባንክ በሚያደርግላት ድጋፍ በየትኛው የልማት አካባቢ ውጤታማ የሆነ እድገት አሳይታለች ለተባለውም ሚስተር ዞሊክ፣ "ኢትዮጵያ በተመረጡና በተለያዩ አካባቢዎች ብቻ ሳይሆን በሁሉም ውጤታማ መሆኗን አሳይታለች፤ የኢትዮጵያ የልማት ስትራቴጂና አቅጣጫዎች ለሌሎች አገሮች ልምድ ለማስተላለፍ የሚያስችል" ነው ብለዋል፡፡

ከጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ጋር ባደረጉት ውይይትም በኢትዮጵያ ባሉ የኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ በስፋት መወያየት እንደሚፈልጉ ተናግረዋል፡፡

ኢትዮጵያ እያስመዘገበች ያለውን እድገት ለማገዝ ጥሩ አጋሮች ለመሆን ምን ማድረግ እንደሚገባቸው እያሰቡ መሆኑን ተናግረው በዋናነት የኢትዮጵያ መንግሥት እድገቱ ሁሉንም አካባቢዎች ያቀፈ እንዲሆን አመራርን ወደ ታች በማውረድ በኩል ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡

በኢትዮጵያ ያለው የእድገት ሁኔታ ጠንካራ እንደሆነ የተናገሩት ፕሬዚዳንት  ዞሊክ ከኢትዮጵያ ጋር በሚኖረው ማናቸውም ጉዳዮች ጠንካራ ግንኙነት እንደሚፈጥር ተናግረዋል፡፡
 
< Prev   Next >