Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Sunday
Jul 06th
Home arrow Sections arrow የክፍያ ቴሌቪዥን ተጠቃሚዎች...
የክፍያ ቴሌቪዥን ተጠቃሚዎች... Print E-mail
Wednesday, 13 February 2008
Image
ሚስተር ጁሊያኖ ማኪንቶ
የክፍያ ቴሌቪዥን ተጠቃሚዎች ቁጥር ከ10 ሺ እንደማይበልጥ ተጠቆመ


በኢትዮጵያ ከ1.5 ሚሊዮን ባለቀለም ቴሌቪዥኖች ሲኖሩ የክፍያ ቴሌቪዥን አገልግሎት ተጠቃሚ የሆኑት ከ10 ሺህ እንደማይበልጡ ተገለፀ፡፡ በአፍሪካ ከሚገኙት 40 ሚሊዮን የባለቀለም ቴለቪዥን ተጠቃሚዎች 1 በመቶ የሚሆኑት ብቻ አገልግሎቱን ያገኛሉ፡፡
የጂቲቪ የክፍያ ቴሌቪዥን አገልግሎት ማኔጂንግ ዳይሬክተርና መስራች ሚስተር ጁሊያኖ ማኪንቶ የጂቲቪ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን በማስመልከት ሰኞ የካቲት 3 ቀን 2000 ዓ.ም በሸራተን አዲስ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ በኢትዮጵያ የክፍያ ቴሌቪዥን ተጠቃሚዎች ቁጥር አነስተኛ መሆን ለዚህም ዋጋው ከፍተኛነትን በምክንያትነት ገልፀዋል፡፡

ጂቲቪ የክፍያ ቴሌቪዥንን ሕብረተሰቡ መግዛት በሚችልበት አቅም ለማቅረብ ማቀዱን የገለፁት ሚኒስትር ጁሊያኖ በሌሎች የአፍሪካ አገሮች እነደሚደረገው ሁሉ ለኢትዮጵያ ስፖርት ድጋፍ ለማድረግ ከፌዴሬሽኑ ኃላፊዎች ጋር መነጋገራቸውንም ጠቁመዋል፡፡

የቀጥታ የስፖርት ዝግጅቶች፣ ወቅታዊ የሆኑ ፊልሞችን፣ የሙዚቃ፣ የዜና ቻናሎችን ለሕፃናት የካርቶን ፊልሞችን ያቀፉ ቻናሎችን ተግባራዊ ማድረጋቸው ተገል"ል፡፡

በአሁኑ ሰዓት አስራ ሰባት ቻናሎች መክፈታቸውን ገልፀው እስከ ግንቦት መጀመሪያ ተጨማሪ 30 ቻናሎችን ለመክፈት መታቀዱንም ገልፀዋል፡፡

ጂቲቪ የባርክሌይን ፕሪምየርሊግ ሲያስተላለፍ የቆየ ሲሆን ከሚቀጥለው ሲዝን ጀምሮ ኤፍ ኤ ካፕን ለአፍሪካ ማድረስ ይጀምራል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ከአውሮፓ እግር ኳስ የጣሊያን ሴሪ ኤን፣ የጀርመን ቡንደስ ሊጋንና የፈረንሳይ ካፕን በመላው አፍሪካ ሲያሰራጭ ቆይቷል፡፡

የሜትሮ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር የሕዝብ ግንኙነትና የማርኬቲንግ ኃላፊ የሆኑት አቶ ዲኒር አብዱላሂ በበኩላቸው ጂቲቪ ቀደም ባሉት ጊዜያት ኢትዮጵያ የነበራትን የረሃብና አስከፊ ገፅታ በመቀየር በኩል ትልቅ እገዛ እንደሚኖረው ገልፀው በአፍሪካ ዙሪያ የሚያጠነጥን ጂ አፍሪክ የተሰኘውና በቀጣይነት የሚከፈተው የጂቲቪ ቻናል የአፍሪካ እሴትን ለማስተዋወቅ እንደሚረዳ ገልፀዋል፡፡  

በቤዛዊት ሥዩም
 
< Prev   Next >