| አዲሱ የፖስታ አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ... |
|
|
| Wednesday, 20 February 2008 | |
|
አዲሱ የፖስታ አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ የሠራተኛ ሽግሽግ ጀመሩ
በቅርቡ የፖስታ አገልግሎት ድርጅት ሥራ አስኪያጅ ሆነው የተሾሙት አቶ ግደይ ገብረዮሐንስ በድርጅቱ ውስጥ የሠራተኛ ሽግሽግ መጀመራቸውን ከድርጅቱ ያገኘነው መረጃ አመለከተ፡፡ በሥራ አስኪያጁ የሠራተኛ ሽግሽግ መሠረት በድርጅቱ የእቅድና ዝግጅት ግምገማ ክፍል ኃላፊ የነበሩት አቶ ሰይድ ከድር ከኃላፊነታቸው ተነስተው በኤክስፐርት ደረጃ እንዲሰሩ ሆኗል፡፡ የድርጅቱ የድጋፍ ሰጪ የሥራ አስፈፃሚ የነበሩት አቶ በዛብህ አስፋው በአቶ ታደለ አስፋው መተካታቸው ታውቋል፡፡ የኢ.ኤም.ኤስ ሥራ አስኪያጅ የነበሩት አቶ ግዛቸው ወርቁ በወይዘሪት ይፍቱሥራ መኮንን ሲተኩ፣ የደብዳቤ አሰራር የሥራ ሂደት ሥራ አስኪያጅ የነበሩት አቶ ፋንታበል አበበ በአቶ በዛብህ አስፋው ተለውጠዋል፡፡ በድርጅቱ የማርኬቲንግና ቢዝነስ ዲቨሎፕመንት ማኔጀር የነበሩት አቶ ቢያዝንልኝ አስረስ ከኃላፊነታቸው ተነስተው በወይዘሪት ይፍቱሥራ መኮንን ቦታ ወደ ፋይናንሺያል ቢዝነስ የሥራ ሂደት መደብ ተመድበው እንዲሰሩ መደረጉ ተጠቁሟል፡፡ በሽግሽጉ ከኃላፊነታቸው የተነሱት አቶ ግዛቸው ወርቁና አቶ ፋንታበል አበበ በምንም ሥራ አልተመደቡም፡፡ አንዳንድ የድርጅቱ ሠራተኞች ሽግሽጉን አስመልክተው ቀደም ሲል የነበሩት ሥራ አስኪያጅ የሠሩትን ስህተት እንዳይደገም አሳስበዋል፡፡ ሠራተኞቹ አይይዘው አዲሱ ሥራ አስኪያጅ የጀመሩት ሽግሽግ አግባብ ቢሆንም በወሳኝ ክፍሎች ላይ የተደረገው ምደባ እንደገና እንዲታይ ጠይቀዋል፡፡ በአሰግድ ተፈራ |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Forums |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Contact Us |