| ዶ/ር አሸብር ለፓርላማ ይወዳደራሉ |
|
|
| Wednesday, 20 February 2008 | |
|
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት የነበሩት ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ ለተወካዮች ምክር ቤት አባልነት የግል ተወዳዳሪ ሆነው እንደሚቀርቡ ተገለፀ፡፡
ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ በወረዳ አስራ ስምንት (ሪቼ አከባባቢ) የምርጫ ክልል በግል ለመወዳደር የሚስችላቸውን መስፈርት አሟልተው የእጩነት መታወቂያ እየተጠባበቁ መሆኑን ከምርጫ ክልሉ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ ዶ/ር አሸብር በምርጫ ሕጉ መሠረት የግል ተወዳዳሪዎች ሊያሟሏቸው የሚገቡትን መስፈርቶች አሟልተዋል፡፡ ከአንድ ሺህ በላይ የአካባቢው ነዋሪዎች በአካባቢው ነዋሪ ስለመሆናቸው የፊርማ ማረጋገጫ በማሰባሰብ ለምርጫ ጣቢያው አስገብተዋል፡፡ በምርጫ ሕጉ መሰረት ከአንድ ሺህ በላይ ፊርማ ያሰባሰቡት ዶ/ር አሸብር በአሁኑ ደረጃ ተጠቋሚ እጩ መሆናቸው ተገል"ል፡፡ ዶ/ር አሸብር ላለፉት ሁለት ዓመታት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንን በፕሬዚዳንትነት ሲመሩ ቆይተው በቅርቡ ከኃላፊነታቸው ቢነሱም ሕጋዊ ፕሬዚዳንት እንደሆኑ በመጥቀስ ለፊፋ ያቀረቡት ክስ ውሳኔ እንዳልተሰጠው ይታወቃል፡፡ በተሾመ ንቁ |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Forums |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Contact Us |