Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Sunday
May 18th
Home arrow Sections arrow ወፎች ከገጠር ወደ ከተማ እየተሰደዱ ነው
ወፎች ከገጠር ወደ ከተማ እየተሰደዱ ነው Print E-mail
Sunday, 06 January 2008
ቢቢሲ አንድን ጥናት መሠረት አድርጐ ሰሞኑን እንደዘገበው ግንደ ቆርቁሮች በእርሻ ማሣዎች ለውጥ ምክንያት ከገጠር ወደ ከተማ እየተሰደዱ ነው፡፡

በገጠር አካባቢ አዕዋፋትን የመመገብ ባህል መዳበርም ሌላው ወፎችን ወደ ከተማ እንዲፈልሱ ምክንያት ነው ብሏል ቢቢሲ በዘገባው፡፡

የእንግሊዝ ፣ትረስት ፎር አሪንቶሎጅ፣ ጥናት እንደሚያመለክተው 46 በመቶ ግንደቆርቁሮች በለንደን አፀዶች የሚገኙ ሲሆን በገጠራማው ክፍል ግን 27 በመቶ ብቻ ይገኛል፡፡ ይህንንም ..አስገራሚ.. ብሎታል አጥኚ ቡድኑ፡፡

ባለፉት አሥርት ዓመታት እንዲህ አልነበረም በተባለው የወፎቹ ፍልሰት አራት ዓይነት ዝርያ ያላቸው ግንደ ቆርቁሮች የበለጠውን ቦታ ይይዛሉ፡፡ ከለንደን በተጨማሪ በማንችስተር 61 በመቶ ይሸፍናሉ፡፡

የአጥኚ ቡድኑ መሪ ፓልሰታን ክሊፍ እንደገለፁት ..በጣም የሚያስገርመው የወፎች ስደት ከገጠር ወጥተው በከተማ መንገዶች ዳር ባሉ አፀዶች እንዲሰፍሩ እያደረገ ነው.. ብለዋል፡፡

እንግሊዝ በክረምት ከሦስት ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ጥንድ ወፎች እንደመኖሪያ እንደምታገለግል ዘገባው አክሎ ገልጿል፡፡

 
< Prev   Next >