|
Sunday, 24 February 2008 |
|
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሳይንስ ፋኩልቲ በማታው ክፍለ ጊዜ ለመጀመሪያ ጊዜ የዲግሪ መርሃ ግብር በ1997 ዓ.ም ትምህርታቸውን ጀምረው በፋኩልቲው በ1999 ዓ.ም ለመመረቅ የበቁት ኤዱኬሽናል ማቲማቲክስ ተማሪዎች ብቻ ነበሩ፡፡
ዩኒቨርሲቲው መውሰድ ያለባቸውን ኮርስ ማጠናቀቃቸውን አውቆ እንዲመረቁ ቢያደርግም ጊዜያዊ ዲግሪያቸውንና ስቱደንት ኮፒ እንዳይወስዱ እገዳ ካደረገባቸው ስድስተኛ ወራቸውን ይዘዋል፡፡ የሚጠበቅባቸውን ማንኛውንም ክፍያም ሆነ መውሰድ ያለባቸውን ኮርስ በሙሉ የወሰዱትና የከፈሉት ዩኒቨርሲቲው ባወጣው መመሪያ መሰረት ነው፡፡ የእነዚህ ተማሪዎች የሶስት ዓመታት የጥረታቸው ውጤት በዩኒቨርሲቲው የተሳሳተ አሰራር በእንጥልጥል ላይ የሚገኝ በመሆኑ ሌሎቻችንን በስጋት እንድንማር አድርጎናል፡፡ እንደሚታወቀው ማንኛውም ተማሪ በየዲፓርትመንቱ መውሰድ ያለበትን ኮርስ የሚወስነው ዩኒቨርሲቲው ባወጣው ዝርዝር መመሪያ መሠረት ነው፡፡ ይህ ሆኖ እያለ ዩኒቨርሲቲው አስተምሮ በህጋዊ መንገድ ካስመረቃቸው ተማሪዎች ዳግመኛ ምን እንደሚፈልግ ግልጽ አይደለም፡፡
(ከዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ) |