| ሴቶች ከወንዶች የበለጠ የማስታወስ ችሎታ... |
|
|
| Sunday, 24 February 2008 | |
|
ሴቶች ከወንዶች የበለጠ የማስታወስ ችሎታ እንዳላቸው ተረጋገጠ
ሴቶች ከወንዶች የበለጠ የማስታወስ ችሎታ እንዳላቸው በሳይንስ ተረጋገጠ፡፡ የስነ ልቦና ባለሙያዎችን ጥናት ጠቅሶ “ሳይንስ ዴይሊ” እንደገለፀው የሰዎች ፆታ መለያየት የእለት ተዕለት እንቅስቃሴያቸውን በማስታወስ በኩል የተለያየ ችሎታ እንዲኖራቸው ምክንያት ሆኗል፡፡ የጥናቱ ውጤት ሴቶች የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴያቸውን ከወንዶች ይልቅ ረዘም ላለ ጊዜ ማስታወስ እንደሚችሉ ይጠቁማል፡፡ ጥናቱ የተደረገባቸው ሴቶች ቃላትን፣ ቁሳቁሶችን፣ ስዕሎችንና የዕለት ተዕለት ድርጊቶችን ከወንዶች በተሻለ ያስታወሱ ሲሆን ወንዶች ደግሞ በቃላት የማይገለፁ መረጃዎችን ወይም ተምሳሌታዊ ነገሮችን በማስታወስ የተሻሉ ሆነው ተገኝተዋል፡፡ በተጨማሪም ሴቶች አንዴ ያዩዋቸውን ሰዎች ፊት የማስታወስ ችሎታቸው ከፍ ያለ መሆኑ ተረጋግጧል፡፡ ለዚሁም ምክንያቱ ከወንዶች ይልቅ ሴቶችን ትኩረስ ሰጥተው ስለሚመለከቱ ሊሆን እንደሚችል ጥናቱን ጠቅሶ ዴይሊ ሳይንስ ረግቧል፡፡ ጥናቱን ያካሄዱት የሥነ ልቦና ባለሙያዎች በዘር ከሚተላለፍ የችሎታ መለያየቶች በተጨማሪ በሴቶችና በወንዶች መካከል ስላለው የማስታወስ ችሎታ ልዩነት ምክንያቱ ምን እንደሆነ አለመታወቁን ተናግረዋል፡፡ |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Forums |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Contact Us |