Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Friday
Jul 04th
Home arrow Sections arrow በእነአቶ ተስፋዬ ብሩ ላይ ክስ ተመሰረተ
በእነአቶ ተስፋዬ ብሩ ላይ ክስ ተመሰረተ Print E-mail
Wednesday, 27 February 2008
የፌዴራል የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን የቀድሞው የኢትዮጵያ ቴሌኮሙኒኬሽን ኮርፖሬሽን ሥራ አስፈፃሚ በነበሩት በአቶ ተስፋዬ ብሩና በሌሎች ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ላይ በትናንትናው ዕለት  ክስ መሰረተ፡፡
የኮሚሽኑ ዐቃቤ ሕግ በተለያዩ የክስ መዝገቦች ክስ የመሰረተ ሲሆን በትናንትናው ዕለት ባቀረባቸው የክስ መዝገቦች፣ በአንደኛው የክስ መዝገብ 14፣ በሁለተኛው ደግሞ 24 ተጠርጣሪዎችን ከሷል፡፡

የተሰጣቸውን የሥራ ኃላፊነት ወደ ጎን በመተው ያለ አግባብ ሥልጣንን ተጠቅመዋል በማለት ዐቃቤ ክስ የመሰረተባቸው ተጠርጣሪዎች፣ ስምንቱ በከፍተኛ የሥራ ኃላፊነት ላይ እንደነበሩ ዐቃቤ ሕግ በቀረበው የክስ ቻርድ ላይ ጠቅሷል፡፡

ተይዘው ያልቀረቡ ተጠርጣሪዎች እንዳሉ ዐቃቤ ሕግ ለፍርድ ቤቱ ባቀረበው አቤቱታ መሰረት፣ ፎቶግራፋቸው በጋዜጣ እንዲወጣ ቢታዘዝም፣ ዐቃቤ ሕግ “አልደረሰልኝም” በማለቱ በድጋሜ በጋዜጣ እንዲወጣ ትዕዛዝ ተሰጥቷል፡፡

ለሁሉም ተከሳሾች የክስ ቻርድ ከምርመራ ማስረጃዎቹ ጋር ተሰጥቶ፣ የተከሰሱበትን ክስ መልስ ለማዳመጥና ማስረጃ እንዲያቀርቡ ለመጋቢት 8 እና 10 ቀን 2000 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ በመስጠት ችሎቱ ተመላሽ ሆኗል፡፡

በታምሩ ጽጌ

 
< Prev   Next >