| ከወርቅ ጋር በተያያዘ የጂኦሎጂካል ሰርቬይ... |
|
|
| Wednesday, 27 February 2008 | |
|
ከወርቅ ጋር በተያያዘ የጂኦሎጂካል ሰርቬይ ቺፍ ጂኦሎጂስት ታሰሩ
በኢትዮጵያ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ ቺፍ ጆኦሎጂስት አቶ አመንቲ አብርሃም ከወርቅ ጋር በተያያዘ ፖሊስ በቁጥጥር ሥር አደረጋቸው፡፡ የአይን እማኞች ለሪፖርተር እንደገለፁት በጂኦሎጂካል ሰርቬይ በምክትል ኃላፊነት ደረጃ የሚሰሩት አቶ አመንቲ በቁጥጥር ሥር የዋሉት ባለፈው ረቡዕ ቢሯቸው በሥራ ላይ እያሉ ነው፡፡ የፌደራል ስነምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ከወርቅ ጋር በተያያዘ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር እንዲውሉ በጥምረት ከፌደራል ፖሊስና ከዋናው ኦዲተር ጋር እየሰራ ባለው ሥራ ቀደም ሲል ከጂኦሎጂካል ላብራቶሪ ሶስት ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ሥር ማዋሉ አይዘነጋም፡፡ በዚሁ መሠረት ከጂኦሎጂካል ላብራቶሪ ኃላፊው፣ ምክትላቸውና አንድ ኬሚስት በቁጥጥር ሥር ውለው ምርመራ እየተካሄደባቸው ይገኛል፡፡ የፌደራል ስነምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ለምርመራ ሥራው ይረዳው ዘንድ ከላብራቶሪ በተለያዩ ወቅት ሙያዊ አስተያየት በመጠየቅ መረጃ ሲያሰባስብ እንደነበርም ከዜናው ምንጮች ለመረዳት ተችሏል፡፡ ከወርቅ ማጭበርበር ጋር በተያያዘ ተጠርጣሪዎች ከብሄራዊ ባንክ፣ ከፖሊስ፣ ነጋዴዎችና አበሮቻቸው በተለያዩ ጊዜያት በቁጥጥር ሥር መዋላቸው የሚታወቅ ሲሆን ፖሊስ ከወንጀሉ ጋር በተያያዘ ተፈላጊ ያላቸውን ለህዝብ ይፋ በማድረግ ድጋፍ መጠየቁም አይዘነጋም፡፡ በአሰግድ ተፈራ |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Forums |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Contact Us |