| አስተዳደሩ በድክመቱ ላይ ትኩረት ያድርግ |
|
|
| Wednesday, 27 February 2008 | |
|
በሪፖርተር ጋዜጣ የካቲት 16 ቀን 2000 እትም እኔ የምለው ገጽ ..አዲስ አበባን የገደላት ሥራ ወይስ ወሬ.. በሚል ርዕስ ከአዲስ አበባ ጊዜያዊ ባለአደራ አስተዳደር የማስታወቂያና ባህል ቢሮ የቀረበውን የመልስ ጽሑፍ አንብቤዋለሁ፡፡ ከቢሮው የቀረበው ይህ ጽሁፍ አትንኩኝ ባይነትን ያንጸባረቀ፣ በአስተዳደሩ ላይ በገሃድ የሚታዩትን የመልካም አስተዳደር እጦትና ሙስናን ሸፋፍኖ ያለፈ ነው፡፡
ከመሬት ጋር በተያያዘ በርካታ ሙስናዎች በመፈጸማቸው በቁጥጥር ስር የዋሉ በርካታ ኃላፊዎች መኖራቸው እንዴት ተዘነጋ? ከቀበሌ እስከ ክፍለ ከተማና እስከ አስተዳደሩ ድረስ በመልካም አስተዳደር እጦት ሳቢያ የሚጉላሉ ባለጉዳዮች ችግር ምን ዓይነት መፍትሄ ተበጀለት? የጊዜያዊ ባለአደራ አስተዳደሩ ኃላፊነቱን ሲረከብ በጅምር የነበሩትን የጋራ ቤቶች ተረክቦ ዳር ማድረሱ አይካድም፡፡ ጥያቄው ግን ሁሉም ቤቶች በትክክልና በአግባቡ ለተጠቃሚዎች ተዳርሰዋል ወይ የሚለው ነው፡፡ ማግኘት የሚገባው ያጣበት፣ ማጣት የሚገባው ያገኘበት እንቅስቀሴ የለም? ከተማዋንም ለነዋሪዎቿ ምቹ የማድረጉ ሥራ በስፋት እንደተከናወነ አድርጎ መጻፉ ..አይናችሁን ጨፍኑና ላሞኛችሁ.. ዓይነት ነው፡፡ ምክንያቱም በገሃድ የሚታየው ከተማዋ ፅዳቷ እየተጠበቀ ሳይሆን የደረቅ ቆሻሻ መከማቻና የፍሳሽ ቆሻሻ መተላለፊያ መሆኗ ነው፡፡ ..የደረቅ ቆሻሻ ማንሻ ያለህ?.. እያለች በመጮህም ላይ ነች፡፡ የከተማው አስተዳደር አንዳንድ ጠንካራ ጎኖቹን ጠቃቅሶ ከመኩራራቱ ይልቅ ደካማ ጐኑን እየዳሰሰ ዕድሜ እስከሰጠው ዕለት ድረስ ጠንክሮ ቢንቀሳቀስ መልካም ነው፡፡ (አብርሃም ኃይሌ፣ ከፒያሳ) |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Forums |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Contact Us |