| በአፋር የቱሪስቶች ጠለፋ ሙከራ ሁለት... |
|
|
| Sunday, 02 March 2008 | |
|
በአፋር የቱሪስቶች ጠለፋ ሙከራ ሁለት ሹፌሮች የገቡበት አልታወቀም
በቅርቡ በአፋር ክልል ዳሎል አካባቢ በጉብኝት ላይ የነበሩ 28 ፈረንሳዊ ቱሪስቶችን ለማገት የተደረገው ሙከራ እንደከሸፈ እና ቱሪስቶቹ በደህና ወደ አዲስ አበባ እንደተመለሱ በተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን የተገለፀ ቢሆንም ቱሪስቶቹን ይዘው ሲንቀሳቀሱ የነበሩት ሁለት ኢትዮጵያውያን ሾፌሮች የት እንደደረሱ እስካሁን አልታወቀም፡፡ ቱሪስቶቹን ያስጐበኝ የነበረው ዴይዚ ቱር ተቀጣሪ የሆኑት ኤርሚያስ አስራት እና ጉዲና መዐዛ የጠለፋ ሙከራ ከተደረገበት ረቡዕ የካቲት 12/2000 ዓ.ም ጀምሮ የደረሱበት አልታወቀም፡፡ ከአካባቢው የተገኘ መረጃ እንደሚጠቁመው ሁለቱ ኢትዮጵያዊያን ሹፌሮች የጠለፋ ሙከራውን ባካሄዱት ታጣቂዎች ተይዘው ወደ ኤርትራ ግዛት ተወስደዋል፡፡ የኤርሚያስ አስራት ቤተሰቦች ለሪፖርተር ጋዜጣ እንደገለፁት ስለ ኤርሚያስ የጠለፋ ሙከራው ከተደረገበት ጊዜ ጀምሮ የሰሙት ነገር እንደሌለ እና ጉዳዩንም ለመንግሥት አመልክተዋል፡፡ ቱሪስቶቹ በሠላም ወደ አዲስ አበባ መመለሳቸው ተገል”ል፡፡ ለጠፉት ኢትዮጵያኖች ጉዳይ ግን በቂ ትኩረት አልተሰጠም፡፡ ይሄኔ የጠፉት የውጪ ሀገር ዜጐች ቢሆኑ ኖሮ ትልቅ የመወያያ ርዕስ ይሆን ነበር ብለዋል፡፡ የዴይዚ ቱር ኃላፊዎች በስልክ ለማነጋገር ሞክረን ጉዳዩ በመንግሥት የተያዘ በመሆኑ መግለጫ አንሰጥም ብለዋል፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ ዋህድ ብርሃኔ ጉዳዩን መንግሥት በመከታተል ላይ እንደሆነ እና አዲስ ነገር ሲኖር ይፋ እንደሚደረግ ገልፀዋል፡፡ ከጠለፋው ሙከራ በኋላ ቱሪስቶቹ ወደ አዲስ አበባ በሠላም ተመልሰው ደቡብ ኢትዮጵያን ሲጐበኙ ሰንብተዋል፡፡ በቃለየሱስ በቀለ |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Forums |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Contact Us |