| ኒያላ ኢንሹራንስ የገዛውን ህንፃ... |
|
|
| Sunday, 02 March 2008 | |
ኒያላ ኢንሹራንስ የገዛውን ህንፃ እንዲመልስ ተፈረደበትኒያላ ኢንሹራንስ ከሰባት ዓመት በፊት ገዝቶት የነበረውን ሆማ ህንፃ ለባለቤቱ እንዲመልስ ተፈረደበት፡፡ የከፍተኛው ፍርድ ቤት ቀጥተኛ ክስ 8ኛ ችሎት ትናንት ባስተላለፈው ውሳኔ መሰረት ኒያላ ኢንሹራንስ በ1994 ዓ.ም በ6.5 ሚሊዮን ብር የገዛውን ሆማ ህንፃን ለባለቤቱ እንዲመልስና የሆማ ህንፃ ባለቤት ደግሞ የወሰዱትን ብር ለኒያላ ኢንሹራንስ እንዲመልሱ ውሳኔ አስተላልፏል፡፡ ኒያላ ኢንሹራንስ ከስድስት ዓመት በፊት የገዛውን ህንፃ እንዲመልስ የተፈረደበት የግዥ ስምምነቱ በመንደር ውል ብቻ የተፈፀመ ውልና ማስረጃ ያላፀደቀው በመሆኑ ነው፡፡ ይህ ውሳኔ የተላለፈው የማይንቀሳቀስ ንብረት ሽያጭ ውል ስልጣን ባለው አካል ፊት ወይም በፍርድ ቤት ፊት መደረግ አለበት በሚለው አንቀጽ 1723 መሰረት መሆኑ ታውቋል፡፡ በመንደር ውል መሰረት የህንፃ ግዥውን የፈፀመው ኒያላ ኢንሹራንስ የህንፃው ባለቤት በውልና ማስረጃ ተገድደው እንዲፈርሙ ያ ካልሆነ ደግሞ ብሩን እንዲመልሱ ለፍርድ ቤቱ ጥያቄ አቅርቦ የነበረ ሲሆን የህንፃው ባለቤት በበኩላቸው አንድ የማይንቀሳቀስ ንብረት የሸጠ ሰው እንደ ውሉ እንዲፈጽም የሚገደደው በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ ብቻ መሆኑን በመጥቀስ ተገድደው ውል ለመዋዋልም ሆነ ስም ለማዛወር አንገደድም የሚለውን መከራከሪያ አቅርበው ነበር፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ኒያላ ኢንሹራንስ አምስት አመት ሙሉ ህንፃውን በነፃ ሲጠቀም መቆየቱን ገልፀው ህንፃው ቢከራይ ኖሮ 7.2 ሚሊዮን ብር ሊያስገኝ እንደሚችል በማብራራት ከኪራይ ይገኝ የነበረው ይህ ገንዘብ በኒያላ ኢንሹራንስ እንዲከፈላቸው ጠይቀው ነበር፡፡ የሁለቱንም ወገኖች መከራከሪያ ያደመጠው ፍርድ ቤትም ኒያላ ኢንሹራንስ አሁን የሚጠቀምበትን ህንፃ ለባለቤቱ እንዲመልስ፣ የህንፃው ባለቤት 6.5 ሚሊዮን ብሩን ለኒያላ ኢንሹራንስ እንዲመልስና የጠበቃ ውልም እንዲቻቻሉ ወስኗል፡፡ በኃይሌ ሙሉ |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Forums |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Contact Us |