| አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጻሕፍት... |
|
|
| Sunday, 02 March 2008 | |
|
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጻሕፍት ዐውደ ርዕይና ሽያጭ አዘጋጀ
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጻሕህፍት ዝግጅት ተቋም የመጻሕፍት ዐውደ ርዕይና ሽያጭ ከመጋቢት መባቻ ጀምሮ ለአንድ ሳምንት እንደሚያዘጋጅ አስታወቀ፡፡ ከቀጣዩ ዓመት ጀምሮ ዓለማቀፍ የመጻሕፍት ዐውደ ርዕይና ሽያጭ (ቡክ ፌር) እንደሚያካሂድ ገልጿል፡፡
በዩኒቨርሲቲው የመጻሕፍት ዝግጅት ተቋም ዳይሬክተር ኘሮፌሰር ማስረሻ ፈጠነ በሰጡት መግለጫ በዓይነቱ ልዩ የሆነው ዐውደ ርዕይ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መጻሕፍት ማዕከልና ሌሎች በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የሚገኙ አሳታሚዎች በቅርብ ያሳተሟቸው መጻሕፍት ለእይታ የሚቀርቡበት፣ ደራስያን፣ መጻሕፍት አሳታሚዎች፣ አታሚዎች፣ የመጻሕፍት ሽያጭ መደብሮች፣ የቤተ መጻሕፍት ሠራተኞች ተማሪዎችና ኅብረተሰቡ የሚገናኝበት መድረክና ትልቅ የመጻሕፍት ግብይት የሚደረግበት ዝግጅት መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Forums |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Contact Us |