Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Friday
Jul 04th
Home
አደጋ መከላከል የትራንስፖርት ድርጅቶች... Print E-mail
Sunday, 09 March 2008
አደጋ መከላከል የትራንስፖርት ድርጅቶች አመራረጥ ሥርዓቱ ለሙስና የተጋለጠ ነው

የአደጋ መከላከልና ዝግጁነት ኤጀንሲ ዕርዳታ ለማጓጓዝ በሚያወጣው ጨረታ ከአምስት ድርጅቶች በታች እንደሚያሳትፍ የጨረታ ኮሚቴ አባላት ከሕግና ሥርዓት ውጪ እንደ ቋሚ የሥራ መደብ ማስቀመጡ፣ አዳዲስ የትራንስፖርት ድርጅቶችን የሚያሳትፍ አሠራር አለመዘርጋቱን በመጥቀስ ይኸንኑ ለሙስናና ብልሹ አሠራር የተጋለጠ ሥርዓቱን እንዲፈትሽና እንዲያስተካክል የፌዴራል ሥነ ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ባካሄደው ጥናት ጠቆመ፡፡
 
ከሚሽኑ በኤጀንሲው የዕርዳታ እህል አጓጓዥ ድርጅቶች አመራረጥ ሥርዓት ላይ በቅርቡ ባካሄደው የአሠራር ሥርዓት ማሻሻያ ጥናት ሪፖርት ላይ እንደተመለከተው በኤጀንሲው የበላይ ኃላፊ ሳይፀድቅ የመንግሥትን የጨረታ ሕግና መመሪያ ሳይከተል "ሥራው አስቸኳይ ነው" በሚል ብቻ ከአጓጓዥ ድርጅቶች ጋር ጊዜያዊ ውል ይፈፅማል፡፡ አሸናፊው ድርጅት ሥራውን ካጠናቀቀ በኋላ ቋሚ ውልና ክፍያ እንዲሰራ ሲጠየቅ ከፍተኛ (ጉቦ) ጥያቄ ይቀርባል፡፡

በመንግሥት ግዢ መመሪያ መሠረት የጨረታ ኮሚቴ አባላት የሥራ ዘመን ሁለት ዓመት መሆን እንዳለበት ቢደነግግም የኤጀንሲው ሦስት የጨረታ ኮሚቴ አባላት ከ1989 ዓ.ም ጀምሮ እንደ ቋሚ የሥራ መደብ እንዲሠሩ መደረጉ በጨረታ አፈፃፀም ወቅት አላስፈላጊ ግንኙነቶች እንዲፈጠሩ መንስኤ ሊሆን እንደሚችል ጥናቱ ጠቁሟል፡፡ አሰራሩንም ህገወጥ ብሎታል፡፡

በተጨማሪም በኤጀንሲው የትራንስፖርት አገልግሎት አቅራቢ ድርጅቶች ዝርዝር ወይም ዳታ ቤዝ የሌለው መሆኑ ብቃት ያላቸውን የዕርዳታ እህል አጓጓዥ ድርጅቶች በተገቢው መንገድ በመምረጥ ጥራት ያለው አገልግሎት እንዳይገኝ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማድረጉን ጠቁሟል፡፡

ኤጀንሲው የውስን ጨረታ ተብሎ ከመንግሥት ግዢ መመሪያ አንቀጽ 11 ቢያንስ አምስት አቅራቢ ድርጅቶችን መጋበዝ የሚለውን ድንጋጌ በመጣስ ከአምስት በታች አጓጓዥ ድርጅቶችን መጋበዝ ግዢ መፈፀምና በተደጋጋሚ የተለመዱ ድርጅቶችን ብቻ አሸናፊ አድርጎ መምረጡ አዲሶቹን አጓጓዥ ድርጅቶች የማያሳትፍ አሠራር እንዲከተል ምክንያት መሆኑ በጥናቱ ጠቁሟል፡፡

በሌላም በኩል ኤጀንሲው ለረዥም ጊዜ ለተረጂዎች እህል ሲያመላልሱ የነበሩና እህል በመስረቅ፣ በማሰረቅና በአግባቡ ለተረጂው ባለማድረስ በወንጀል የተጠየቁ የትራንስፖርት ድርጅቶችን ከጨረታው እንዲገለሉ አያደርግም ሲል በተደጋጋሚ ክስ የተመሰረተበትን የትራንስፖርት ድርጅት ስም በመጥቀስ አሰራሩን ወቅሷል፡፡

የፌዴራል ስነምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ አሊ ሱሌይማን፣ የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር ክቡር አቶ ሲሞን መቻሌና አግባብ ያላቸው የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት የካቲት 13 ቀን 2000 ዓ.ም ውይይት አካሂዷል፡፡ በውይይቱ ኤጀንሲው የመንግሥትን የግዢ መመሪያ ከመከተል ውጪ ሌላ አማራጭ እንደሌለ ታምኖበታል፡፡  

ኮሚሽኑ በጥናቱ ለጠቀሳቸው ችግሮች ባሰፈረው መፍትሄም ኤጀንሲው በዋንኛነት የመንግሥት ግዢ ሕግና መመሪያ አክብሮ እንዲሠራ መክሯል፡፡ በተጨማሪም ኤጀንሲው የዕርዳታውን ዓይነት መደበኛ እና አስቸኳይ በሚል በመለየት ለመደበኛ ዕርዳታ አጓጓዥ ድርጅቶች የግልፅ ጨረታ ዘዴ የተከተለ ግዢ መፈፀም እና ለአስቸኳይ ዕርዳታ ደግሞ አስቸኳይ መሆኑን ለማረጋገጥ የሚያስችል የመመዘኛ መስፈርት በማስቀመጥ እንዲተገብር አሳስቧል፡፡  

በጋዜጣው ሪፖርተር
 
< Prev   Next >
Headline
  • Pause
  • Previous
  • Next
1/10
በፕሬስ ሕጉ ላይ የሚወያይ ስብሰባ ተጠርቷል
በጋዜጣው ሪፖርተር

በትናንትናው ዕለት በፓርላማ በፀደቀው የመገናኛ ብዙሃንና የመረጃ ነፃነት ሕግ ላይ የሚወያይ ወርክሾፕ በዛሬው እለት በጊዮን ሆቴል መጠራቱን አዘጋጆቹ አስታውቀዋል፡፡

Read more...
 
Zena
Image አወዛጋቢው የፕሬስ ህግ ፀደቀ
"የዜጎችን መረጃ የማግኘት መብት የሚገድል አዋጅ ነው" አቶ ተመስገን ዘውዴ
"እኔና እንደኔ የሚያስቡ ሰዎች ይህን ቀን በሀዘን ነው የሚያዩት" አቶ ቡልቻ ደመቅሳ

Editorial
Image ከፕሬስ ነፃነት ሽሽት
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በቅርቡ ከኒውስዊክ መፅሔት ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ የሚፀድቀው የፕሬስ ሕግ ኢትዮጵያን በፕሬስ ነፃነት መስፈርት በዓለም አሉ ከተባሉት በግንባር ቀደምትነት የሚያሰልፋት ይሆናል ብለው ቃል ገብተውልን ነበር፡፡ ትናንት የፀደቀው ግን ኢትዮጵያን በፕሬስ ነፃነት ግንባር ቀደም የሚያደርጋት ሳይሆን ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባት ነው፡፡ ቃል የተገባልን ሌላ የፀደቀው ሌላ!

 
Politics
የአዲሱ የተቃዋሚ ፓርቲ ዳዴ
በሰለሞን ጎሹ

ባለፈው እሁድ ሰኔ 22 ቀን 2ዐዐዐ ዓ.ም. በኢየሩሳሌም ሆቴል የስብሰባ አዳራሽ ብርሃን ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ፓርቲ የመጀመሪያውን ጠቅላላ ጉባዔ አካሂዷል፡፡ ፓርቲው በእለቱ የቀድሞውን የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት ምክትል ኘሬዚዳንት አቶ ሙላቱ ጣሰውን ኘሬዚዳንት አድርጎ መርጧል፡፡

Briefs
ከ3ሺ 400 በላይ የቀበሌ ሥራ አስኪያጆች ተመደቡ
በደቡብ ክልል በቀበሌ ደረጃ መልካም አስተዳደርን በማስፈን ሕዝቡ ቀልጣፋና ፈጣን የመንግስት አገልግሎት እንዲያገኝ ለማስቻል ከ3.ሺ 400 በላይ የቀበሌ ሥራ አስኪያጆች መመደባቸውን የክልሉ አቅም ግንባታ ቢሮ አስታወቀ፡፡

 
Business & Economy
Image የብሔራዊባንክ ረቂቅአዋጅ አሁንም እያነጋገረ ነው
በዳዊት ታዬ

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የተዘጋጁት የባንክ ሥራና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ረቂቅ አዋጆች ወደ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተሸጋግረዋል፡፡

Shemach
የከርሞ ገበያን ለማረጋጋት
በናታን ዳዊት

በርካታ የአገራችን አርሶ አደሮች ዓመታዊ ምርታቸውን ለማምረት ማዳበሪያ መጠቀም ከጀመሩ ቆይተዋል፡፡ ያለ ማዳበሪያ መሬቱ አልሰጥ ብሏል፡፡ በዚህም የተነሳ አርሶ አደሮቻችን ማዳበሪያን እንደዋና የምርት ግብዓታቸው አድርገው ይወስዳሉ፡፡ በየዓመቱ ወደ አገር ውስጥ የሚገባው የማዳበሪያ መጠን እየጨመረ መምጣቱም የተጠቃሚዎች ቁጥር እየበረከተ መሆኑን ያሳየናል፡፡

 
Interview
"እንደ እንጉዳይ በአጭር ጊዜ ውስጥ...
"እንደ እንጉዳይ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሊደርስ የሚችል የምግብ ዘር የለም"
ዶ/ር ዳዊት አባተ

እንጉዳይ በውስጡ ፕሮቲን፣ አሚኖ አሲዶች፣ ሚኒራሎች0ቫይታሚኖች፣ የያዘ ሲሆን እንዲሁም በምግብ አጣፋጭነቱና በመድሃኒትነቱ ይታወቃል፡፡ እንጉዳይን በጥናት በተደገፈ መልኩ ለማምረትና ለምግብነት ለማዋል በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ባዮሎጂ ዲፓርትመንት አነሳሽነት ጥናት ማድረግ የተጀመረው ከ10 ዓመታት በፊት ነበር፡፡ በአሁኑ ጊዜ ጥናቱ ውጤታማ ሆኖ ኦይስተር፣ ሽታኪ፣ በተን እና ናሜኩ የተባሉትን አራት ዓይነት ለምግብነት የሚውሉ የእንጉዳይ ዓይነቶች በኢትዮጵያ በመጠኑ ማምረት ተጀምሯል፡፡

Fermata
የመጀመሪያዎቹ
ዳግማዊ አጤ ምኒልክ በ1896 ዓ.ም የመንገድ መዳመጫ ሩሎ እና ሰረገላ አስመጥተው የመንገድ ሥራ አስጀመሩ፡፡ የመጀመሪያውም መንገድ 56 ኪ.ሜ ርዝመት ያለው ከአዲስ አበባ እስከ አዲስ ዓለም ድረስ የተሰራው ነው፡፡

 
Kibur Minister
ክቡር ሚኒስትር
(ሥራ አስኪያጁ፣ በሚኒስትሮች የሚታዘዙ ሳይሆኑ ሚኒስትሮችን የሚያዙና በሚኒስትሮች የሚፈሩ ናቸው)

Life & Art
Image ሰንደቅ ዓላማችን
በሔኖክ ያሬድ

"በባንዲራ"" በባንዲራ"" በባንዲራችን"" በሕግ ቁም ብዬሃለሁ!!" ትለዋለች፤ እየተከተለች፡፡ አዲስ አበባ ውስጥ፣ ወደ ቀጨኔ መድኃኔዓለም በሚወስደው መንገድ፣ ድልድዩ አጠገብ፣ ከአባ ሀብቴ ቤት አጠገብ ነው፡፡ ሴትየዋ ጠላ ሻጭ ናት፡፡

 
Social
Image “ኮትቻ የዋለ ምሳና ራቱን አያጣም”
በምሕረት ሞገስ

አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የቀድሞው የባንክ ባለሙያዎች ማሰልጠኛ ተቋም አካባቢ የሚገኙ የተለያዩ የመኖሪያ ቤት ግንባታዎች አብዛኞቹ ግንባታቸው ተቋርጧል፡፡ አካባቢው ጭር ብሎ የሚታየው መሠረታቸው ወጥተው የቆሙ ጅምር ግንባታዎች ናቸው፡፡ አንዳንዶቹ ግንባታዎች መጀመሪያና ሁለተኛ ፎቅ ድረስ ደርሰው ቆመዋል፡፡

Science & Technology
የሚበር መኪና እውን ሊሆን ነው
የቤት ውስጥ ኮምፒውተርና በኤሌክትሪክ የሚሰራ መኪና በመስራት የሚታወቁት ክሊቭ ሲን ክላር ለቢቢሲ ሬድዮ እንዳስታወቁት ለረዥም ዓመታት ሲያልሙት የቆዩት በአየር ላይ መብረር የሚችል መኪና እውን ሊሆን ነው፡፡ እሳቸው እንደሚሉት “በአየር ላይ የሚበር መኪና ለመስራት በኢኮኖሚም ሆነ በቴክኒክ የሚቻል ነው”

 
Diaspora
Image የዲያስፖራውን መረጃ የማሰባሰብ...
የዲያስፖራውን መረጃ የማሰባሰብ ሥራ እየተከናወነ ነው

በምሕረት ሞገስ

በርካታ ኢትዮጵያውያን በሚገኙባቸው የውጭ አገሮች ዲያስፖራውን አስመልክቶ መረጃ የማሰባሰቡ ሥራ እየተከናወነ መሆኑ ተገልጿል፡፡

Youth
Image “ስለ ምዕተ ዓመቱ የልማት ግቦች...

“ስለ ምዕተ ዓመቱ የልማት ግቦች አለማወቅ አስገራሚ ነው”

በምሕረት አስቻለው

“ወጣቶች የተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች አሉባቸው፡፡ እነዚህን ችግሮች በተለያየ መልኩ ለመፍታት ወጣቶቹ ተደራጅተው በመንቀሳቀስ፣ መንግሥትና ሌሎች አካላት ደግሞ ድጋፍ በማድረግ ላይ ናቸው፡፡

 

 
Opinion
ራዲዮ አክቲቭ ቃላት የሚተፉ ፕሬስማ!!

(አ.አ.)

መጀመሪያ ሀሳብን በነጻ የመግለጽ መብት በኢትዮጵያ የሽግግር መንግሥት ቻርተር ተረጋገጠ ተባለ፡፡ በግንቦት 1983 ዓ.ም እና ያንኑ ያህል አሁን ታሪካዊ እየሆነ በመጣው በጥቅምት 11 ቀን 1985 ዓ.ም መካከል የነበሩት 512 ቀናት (17 ወራት ወይም 73 ሳምንታት) ለሁለት የተከፈለ የተለያዩ አስተያየቶችና አቋሞች የተስተናገዱባቸው ነበሩ፡፡ በአንድ በኩል የፕሬስ ነጻነት ህግን አስፈላጊነትን፤ አምንበታለሁ የሚለው ወገን የፕሬስ ህጉ ዘገየ፣ መሥራት አልቻልንም እያለ ጮኸ ተቃውሞውን ስጋቱን አስተጋባ፡፡

 

Letter to Reporter
ክትትል ይደረግ
የሕክምና ሙያ ከሰው ሕይወት ጋር የተያያዘ በመሆኑ ልዩ ጥንቃቄና ትኩረት የሚሰጠው ጉዳይ ነው፡፡ ይህ አይነቱ ጥንቃቄና ትኩረት የማድረጉ ሥራ ደግሞ ለመንግስት ብቻ የሚተው አይደለም፡፡ ባለድርሻ አካላትና ኅብረተሰቡም ጭምር ሊሳተፉበት ይገባል፡፡ በሕገ ወጥ መንገድና ሙያው ከሚፈቅደው ውጪ የሚንቀሳቀሱ የሕክምና ተቋማትን በመጠቆም ረገድ ኅብረተሰቡ ንቁ ተሳትፎ ማድረግ ይኖርበታል፡፡ ጉዳዩ የሚመለከተውም መንግስታዊ አካል በየወቅቱ ክትትልና ቁጥጥር ማድረግ ይጠበቅበታል፡፡

 
Women
Image ከፈተና ወደ ፈተና
በትዕግሥት ዘሪሁን

እናቷን በሞት ያጣችው ገና በ11 ዓመቷ ነው፡፡ እናቷ ከሞተች በኋላ በእግሯ መራመድ የማትችለውን የሁለት ዓመት እህቷን የእንጀራ አባቷን የመንከባከብ ኃላፊነት ወደቀባት፡፡ እሷ እንደምትለው እቤት ውስጥ የሚያስፈልገውን ስራ ሁሉ የምትሰራው ብቻዋን ነበር፡፡ ቤት ማፅዳት፣ ልብሳቸውን ማጠብ፣ ምግብ ማብሰልና አስፈላጊ የምግብ እህሎችን መግዛት ይጠበቅባታል፡፡

Temuaget
ጓዳችን፣ ማጀታችን፣ በጀታችን፣
"እንዲህ ያለ ነገር የጠፋ ለመላ"?

አብነት ገመቹ

"በጀቱ ለፓርላማው በወቅቱ አልቀረበም፣ የቀረበውም በዝርዝር አይደለም" የሚል አይነት ጥያቄና እንቅፋት ምራቃቸውን የዋጡ ጠያፋቸውን የከተቱ፣ ለበጀት ዲሲኘሊን እና ለሕግ የበላይነት የተገዙ አገሮች ችግር በጭራሽ አይደለም፡፡

 
Law
የዳኞች መርሀ ችሎት
አካለ መጠን ያልደረሱ ወጣቶች የሚፈፅመት ወንጀል
ሥርዓቱን በተመለከተ


1.    ዕድሜው ከ9 እስከ 15 ዓመት የሆነ አካለ መጠን ያልደረሰ ልጅ ከአዋቂዎች ጋር በተከሰሰበት የወንጀል ነገር አብሮ ሊታይ አይችልም (ወ/መ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 5)
Zennk
ሳይቤሪያ
ሳይቤሪያ /በሩሲያንኛ ሲቢር ይባላል/ ከኡራል ተራራዎች በስተምሥራቅ የሚገኝ የእስያን ክፍለ ዓለም መላው ሰሜናዊ ክፍል የሚይዝ በጣም ሰፊ የሆነ ግዛት ነው፡፡

 
Delalaw
እህህ. . .
ከመሬቱ በላይ ትውላለች እሷ
ደግሞም ከእሷ በላይ ይውላል ሰማይ
አልሙት አልጥፋ የእሷን ልክ ሳላይ

Teles
የሕይወት አቅጣጫ ሲቀየር
በትዕግሥት ዘሪሁን

የስምንተኛ ክፍል ትምህርቷን እስከምታጠናቅቅ ድረስ የወላጆቿን ፍቅርና እንክብካቤ እያገኘች በቤተሰቦቿ ቤት ትማር ነበር፡፡ ተወልዳ ባደገችበት ጎንደር ከተማ ከጓደኞቿ ጋር ለዋና ወደ ወንዝ የወረደችበት እለት ግን የህይወቷን አቅጣጫ ቀየረው፡፡ እሷ እንደምትለወ ውሃው ላይ አርፎ የተንፀባረቀው የፀሃይ ጨረር የአይን ብርሃኗን አሳጥቷታል፡፡ ወይንሸት ሙሉሰው ህይወቷ አስቸጋሪ የሆነው ከዚህ አጋጣሚ በኋላ መሆኑን ትናገራለች፡፡

 
Sport
አትሌት አምበሴ ሞርፊን የተሰኘ...
አትሌት አምበሴ ሞርፊን የተሰኘ መድሃኒት ወስዶ ስለተገኘ ሁለት ዓመት ተቀጣ
 
በደረጀ ጠገናው

ኢትዮጵያዊው የማራቶን አትሌት አምበሴ ቶሎሳ ሞርፊን የተሰኘ የፔንኪለር ተመሳሳይ መድሃኒት ወስዷል በሚል አለም አቀፉ አትሌቲክስ ማኅበራት ፌዴሬሽን (አይ.ኤ.ኤ.ኤፍ) አትሌቱን ለሁለት ዓመት ከማንኛውም ውድድር አግዶታል፡፡ አትሌት አምበሴ በበኩሉ በወቅቱ ወስዷል ስለተባለው መድሃኒት ምንም የሚያውቀው ነገር እንደሌለ ገልጿል፡፡

Taxi
የተለመዱ፣ ያልተፈቱ
ለመሳፈር ቅድመ ዝግጅቶችን አጠናቅቀን ታክሲ ተራ ተገኘን፡፡ ታክሲ አገልግሎት ሰጪ እንደመሆኑ፣ አገልግሎት ለመስጠት በቀላሉ አይሆንለትም፡፡ ተራ ይጠብቃል፡፡ የተራ አስከባሪው ፍቃድ ሲገኝ ነው ጭኖ መውጣት የሚቻለው፡፡

 
World
Image "ምዕራባዊያን - ሊሰቀሉ ይችላሉ"
የሙጋቤ ቃል አቀባይ

በጋዜጣው ሪፖርተር

የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ የሁለት ቀኑን ጉባኤ ሲፈፅም በዚምባብዌ የብሔራዊ አንድነት መንግሥት እንዲቋቋም አስተያየቱን ሰጥቷል፡፡ ይሁን እንጂ በስብሰባው ላይ የተገኙት ፕሬዚዳንት ሮበርት ሙጋቤ የሰጡት ምላሽ አልነበረም፡፡ ምናልባትም ቀደም ሲል "የአፍሪካ ሕብረት ምን አገባው? የሚለውን አቋማቸውን ፀንተውበት ሊሆን ይችላል፡፡"

 
  • Do You Know ?
    How To Increase Font Size
    You can increase the font size of the website if it appears smaller than normal. Just click the member area link at the top right of this page and the page will slide down. At the top left corner of the page, look for three small buttons. To increase font size, click the button with "+" sign and "-" sign to decrease font size.
  • Tips !
    Tips for Amharic Version
    • Use Internet Explorer version 6 or better
    • Adjust your screen resolution to 1024 X 768
    • Use the font resizer to increase font size if needed
    • Though it is not strictly needed having power geez unicode font could enhance the font rendering in your browser
 

Important Links

Visit Ethiopian Yellow PagesA forum on Dialogue, Democracy & Development