| ባለቤቱን በአሰቃቂ ሁኔታ ገድሏል... |
|
|
| Sunday, 09 March 2008 | |
|
ባለቤቱን በአሰቃቂ ሁኔታ ገድሏል የተባለ ተጠርጣሪ ተያዘ
በደቡብ ክልል በአላባ ጠንባሮ ከተማ ባለቤቱን በቢላ አርዶ ገድሏል የተባለ ተጠርጣሪ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋለ፡፡ የአላባ ጠንባሮ ከተማ መርማሪ ፖሊስ መቶ አለቃ ኑርዬ ለሪፖርተር ጋዜጣ እንደገለፁት ተጠርጣሪው ግለሰብ በቁጥጥር ሥር የዋለው የካቲት 19 ቀን 2ዐዐዐ ዓ.ም. በባለቤቱ ወ/ሮ ፀሀይን በቢላ አርዶ ከገደለ በኋላ ለማምለጥ ሲሞከር ነው፡፡ እንደ መቶ አለቃ ኑርዬ ገለፃ ግለሰቡ በሁለት ልጆቹ እናት ላይ ወንጀሉን የፈፀመው ሆን ብሎ ነው፡፡ ሟቿ የተገደለችው የልጇን አንደኛ ዓመት በዓል ለማክበር በዝግጅት ላይ በነበረችበት ወቅት መሆኑን የጠቆሙት መርማሪው ፖሊሱ ተጠርጣሪው ግለሰብ በባለቤቱ ላይ ወንጀሉን የፈፀመው ዝግጅቱን በማሰናዳት ሲያግዙ የነበሩ ጐረቤቶችን ምክንያት በመፍጠር ከቤት እንዲወጡ ካደረገ በኋላ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ተጠርጣሪው ግለሰብ በቅናት ተገፋፍቶ ወንጀሉን የፈፀመ መሆኑን የገለፁት መቶ አለቃ ኑርዬ ተጠርጣሪው ለፖሊስ ቃል በሰጠበት ጊዜ ትክክለኛ ያልሆነ የአባትና የአያት ስም አስመዝግቦ እንደነበር ተናግረዋል፡፡ የሟች ወንድም የሆነው ታምራት ከላይ በበኩሉ ለሪፖርተር ጋዜጣ እንደገለፀው ተጠርጣሪው ግለሰብ በፖሊስ የተያዘው ወንጀሉን ፈፅሞ ከቤቱ ሲወጣ ልብሱ በደም ተጨማልቆ የተመለከተ ጐረቤት ለፖሊስ በማመልከቱ ነው፡፡ ከአላባ ጠንባሮ ከተማ ካገኘነው መረጃ ለማወቅ እንደቻልነው የከተማው ነዋሪ ህዝብ ወንጀሉ በተፈፀመ ማግስት ሰላማዊ ሰልፍ በማድረግ በወንጀል ፈፃሚው ላይ ትክክለኛ ፍርድ እንዲተላለፍበት ጠይቋል፡፡ በኃይሌ ሙሉ |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Forums |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Contact Us |