Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Thursday
Aug 28th
Home
የኢኮኖሚ ጭንቅላት ናቸውና... Print E-mail
Sunday, 09 March 2008
Imageየኢኮኖሚ ጭንቅላት ናቸውና ልዩ ትኩረት ለፋይናንስ ተቋማት!

የተዛባና የተነካ ጭንቅላት ያለው ሰው አይ ቁመት፣ አይ መልክ፣ አይ ጥርስ፣ አይ ጠጉር፣ አይ እግር፣ አይ ዳሌ እያሉ ቢያደንቁት ትርጉም የለውም፡፡ እንደ ስሙ ሊያንቀሳቅሰውና ሊያኖረው የሚያስችለው ወሳኙ የሆነው ጭንቅላቱ ተዛብቷልና፡፡
 
ኢኮኖሚም እንደዚያ ነው፡፡ የኢኮኖሚው ጭንቅላት የሆኑት የፋይናንስ ድርጅቶችና ተቋሞች ከቀወሱ ልማትም፣ እድገትም፣ መሠረተ ልማትም፣ ንግድም፣ ኮንስትራክሽንም፣ አገልግሎቱም ይበላሻሉ፡፡ እነዚህ ከተበላሹ ደግሞ አይ የአየር ጠባይ፣ አይ ተራራ፣ አይ ሸንተረር፣ አይ ዘፈን፣ አይ መዝሙር፣ አይ ባህል፣ አይ ታሪክ". እያልን ብናደንቅና ብናወድስ ትርጉም የለውም፡፡ አጉል ማስተዛዘኛ ነው የሚሆነው፡፡

የፋይናንስ ድርጅቶች ስንል ብሔራዊ ባንክ፣ ሌሎች ባንኮችና ኢንሹራንሶች ማለታችን ነው፡፡ የመንግሥትም ይሁኑ የግል የፋይናንስ ተቋሞች በጋራ የኢኮኖሚው ጭንቅላት ናቸው፡፡ የመንግሥትም ሆነ የግል ገንዘብና ንብረት፣ ንግድና ኢንቨስትመንት፣ ኢምፖርትና ኤክስፖርት፣ ኮንስትራክሽንና መሠረተ ልማት የሚንቀሳቀሰው በእነዚህ ተቋማት ዙሪያ ነው፡፡ እነሱ ከቀወሱና ከተናጉ ጠቅላላ የአገሪቱ ኢኮኖሚ ይናጋል፣ ይቃወሳል፡፡

በአሁኑ ጊዜ በአገራችን ያሉት የፋይናንስ ድርጅቶች፡- እጅግ ከፍተኛ ትኩረት፣ ዳግም መደራጀት፣ አዲስ አወቃቀር አዲስ ፖሊሲ፣ አዲስ ራዕይና እምነት ያለው የሰው ኃይል ያስፈልጋቸዋል፡፡ ይህን እውን ለማድረግ መንግሥት ቆራጥና አፋጣኝ እርምጃ መውሰድ ይኖርበታል፡፡ እርምጃውን ለመውሰድ የሚያስችለው በቂ መረጃም በእጁ ይገኛል፡፡

ብሔራዊ ባንክ ብቃት ያለው አመራር እንደሌለው ገሃድ ወጥቷል፡፡ የአገር ሃብትና መጠባበቂያ የሆነው ወርቅ መሣቂያና መቀለጃ ሲሆን ብሔራዊ ባንክ ተባባሪ ሆኗል ወይም ተጭበርብሯል፡፡ በሁለቱም በኩል ሲታይ ብቃት የሌለው ለመሆኑ በቂ ማረጋገጫ ነው፡፡ ልማት ባንክ ከሰረ ብሎ ብሔራዊ ባንክ ያቀረበው ሪፖርትም የልማት ባንኩን ደካማነት ብቻ የሚያሳይ ሳይሆን የብሔራዊ ባንክንም ደካማነት ያረጋግጣል፡፡ ምክንያቱም ይህ ኪሳራ የአንድ ዓመት ሳይሆን ቢያንስ ላለፉት አምስት ዓመታት ሲከማች የመጣ ስለሆነ ብሔራዊ ባንክ በጊዜው ለምን አልገለፀም? አልተቆጣጠረም? የሚያሰኝ ነው፡፡

ለአበባ የተሰጠው ብድር ከስድስት መቶ ሚሊዮን ብር በላይ ሆኖ የተገኘው ገቢ ግን ሰባ ሚሊዮን ብር ብቻ በነበረበት ወቅትም ብሔራዊ ባንኩ እንኳን ሊቆጣጠርና መፍትሔ ሊሰጥ "እንዴት ነው ነገሩ?" የሚል መገረምም አላሳየም፡፡ ሥራ ላይ ሊውል የሚችል ብር ሲቃጠል የሚታይበት ብሔራዊ ባንክ ብሔራዊ ባንክ ሊባል አይገባውም፡፡

የብሔራዊ ባንክ ገዢና ምክትል ገዢ ብቻ ሳይሆኑ ብሔራዊ ባንኩን የሚቆጣጠረው ባለሥልጣንም የሚጠየቅበት ጉዳይ ነው፡፡ ብሔራዊ ባንክ የራሱን ሥራ  ማካሄድ አቅቶት የበላይ አካል ሥራውን እንዲሠራለት ሲጠብቅና ሲማጠን የበላይ አካልም የባንኩን ችግር አይቶ ከመፍታት ይልቅ የባንኩን ሥራ "በአደራነት" እያካሄደ መቆየቱ ያስጠይቀዋል እንጂ አያስመሰግነውም፡፡

የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ኤጄንሲ ኃላፊ አጥቶ ለሦስት ዓመታት ተዘግቶ መክረሙም ተገቢ አልነበረም፡፡ ብዙ መሥራትና ማስተካከል ይችል የነበረ አካል ኃላፊ አጥቶ ሥራ ፈት ሆኖ መቆየቱ ሌላው የፋይናንስ ድርጅቶች ትኩረት የሚያስፈልጋቸው መሆኑ ማረጋገጫ ነው፡፡ በአሁኑ ጊዜ ኤጄንሲው እያደረገው ያለው ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴ ቀደም ብሎ ቢጀምር ኖሮ ብዙ ችግር ማስወገድ በተቻለ ነበር፡፡

የልማት ባንክ ችግር ሲወርድ ሲዋረድ የመጣ ችግር ነው፡፡ ኃላፊዎች ተብለው የተቀመጡ ሰዎች በሚያበድሩት ድርጅት ቦርድ አባላት ሆነው ሲሰሩና ያበደሩት ድርጅት ሊሸጡና ሊለውጡ እንደሚችሉ ውክልና እንዲሰጣቸው ሲጠየቁ እየተስተዋለና እየተነገረ፣ በመገናኛ ብዙሃን እየተላለፈ እያለ ሥራ ጠፍቶ አሁን ልማት ባንክ ችግር ውስጥ ገብቶ ቢገኝ የሚገረም ሰው ካለ ራሱ የሚያስገርም ሰው ነው፡፡ አምስት ቢልዮን ብር አበድሮ ከአምስቱ አራቱ ቢልዮን መሰብሰብ አቅቶት ቢገኝ ችግር ለመኖሩ የሚሰጠው ተጨማሪ መረጃ አይኖርም፡፡ የታወቀ ነውና፡፡ ስለአሟሟቱ የሬሳ ምርመራ ዘዴው እውቀት ይሰጥ እንደሆነ እንጂ፡፡

የባንኮችና ኢንሹራንሶች ፖሊሲ ምን ይመስላል? ኤንትሬና አሮጌ ቪላ አለህ እያሉ ዋስትና (ኮላትራል) ማፈላለግ የዘመናዊ ባንክ አሰራር ነው ወይ? ባንኮች በሃራጅ በሚሸጡት ንብረት ላይ ነው ማተኮር ያለባቸው ወይስ ቢዝነሱ የተሳካ ሆኖ በሚከፈለው ወለድና ብድር? ባንኮች በሚሸጥ ንብረት ላይ እያተኮሩ የሚያበድሩ መሆናቸው ራሱ አሳዛኝ ነው፡፡

በሚሸጠው ንብረት ላይ ያለው ፖሊሲ ምን ይመስላል? መኪኖች (ትናንሽ የቤትና የቢሮ እንዲሁም የጭነት መኪኖች) በባንኮችና በኢንሹራንሶች ተወርሰው ከአዲስ አበባ እስከ አቃቂ ባለው ዋና መንገድ ዳር ተጥለው ዝገው፣ ሣር በቅሎባቸው ይታያሉ፡፡ የፎርክሎዣር ሕግ ውጤቱ ይህ ነው ወይ? ንብረት ወርሶ መጣል፤ ንብረቱም ለኪሳራ፣ ገንዘቡም ለኪሳራ ማድረግ መዳረግ? ከመውረስና ከመጣል ይልቅ ጤናማ ገንዘብ ሰጥቶ በሽተኛውን ገንዘብ ማዳን አይሻልም?

የግል ባንኮች የሚመረቱት አትራፊ ሆነው መስራቾች ከትርፉ እንዲጠቀሙ ሳይሆን ለመበደር እንዲመቻቸው ብለው በመስራቾች ሲመሰረቱ ምን ይባላል? ከእድርና ከእቁብ ያነሰ አደረጃጀትና አመኔታ ያላቸው የግል ባንኮችስ ባንኮች ናቸው? ልማት ላይ ከማተኮር ይልቅ "ገልባጭ" መኪና መግዣ ለማበደር የሚቋቋሙ ባንኮችን ባንኮች እንበላቸው? ጥሩና በልማት ላይ የሚንቀሳቀሱ የሚባሉ ጥቂት የግል ባንኮች አሉ፡፡ በአጠቃላይ ሲታይ ግን ለስርቆትና ለዝርፊያ እንዲመቻቹ የሚቋቋሙ ባንኮች አሉ፡፡ ይህም የፋይናንስ ድርጅቶችን ችግር የሚያረጋግጥ ነው፡፡

ብዙ ለማለት የማስረጃ ችግር የለም፡፡ ነገር ግን በአሁኑ ጊዜ በወርቅም፣ በባሌስትራም፣ በኪሳራውም፣ በትርፉም፣ በገንዘብ እጥረቱም፣ ባልተሰበሰበ ገንዘብ ብዛቱም አንፃር ሲታይ በፋይናንስ ድርጅቶች ዙሪያ ከፍተኛ ችግር እንዳለ ፀሐይ የሞቀው ሐቅ ሆኗል፡፡ አሳሳቢ ነው፡፡ በተለይም ከአሁኑ አሳፋሪ አካሄዳቸው አንፃር ሲታይ እነዚህን ባንኮች ይዞ ልማት አይታሰብም፡፡

ይህ ችግሩን በግልፅ ወደ አደባባይ እንዲወጣ ያመቻቸ ስለሆነ መንግሥት ይህ ሁኔታ ሳያመልጥ በአስቸኳይ እርምጃ ይውሰድ፡፡ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ደመወዝ ለመጨመር ኤጀንሲው የቦርድ አባላትም ማኔጅመንቱም እየተነጋገሩ ሠርተዋል፡፡ ይህ ከተቻለ፣ እየተነጋገሩ ብዙ ችግር መፍታት ይቻላል ማለት ነው፡፡ ይህ አካሄድ ተሳክቶ ብሔራዊ ባንክን የማስተካከል ሥራ ካልተሰካ ግን ታጥቦ ጭቃ ነው፡፡

ስለዚህ፣ መንግሥት ለፋይናንስ ድርጅቶች ጥንካሬና መሻሻል ልዩ ትኩረት ይስጥ፡፡ አሁኑኑ!!
 
< Prev   Next >
Headline
  • Pause
  • Previous
  • Next
1/10
የሪፖርተር ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ በዋስ ተፈታ

ከጋዜጣው ሪፖርተር

የሪፖርተር ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ አማረ አረጋዊ በጎንደር ፖሊስ ጣቢያ የስድስት ቀናት እስራት በኋላ ትላንት ነሐሴ 21/2000 አመሻሽ ላይ ተለቋል፡፡

Read more...
 
Zena
“እስልምና መቻቻል ነው፤...
“እስልምና መቻቻል ነው፤ ሽብርተኝነትን አይወክልም” ሚስ ሳቢን ማሊክ፣ የእንግሊዝ ሴቶች ኮሚሽነር ምዕራባዊያን ተምሳሌት በሆነችው እንግሊዝ ውስጥ በሌላው አገር የማይታይ የሃይማኖት እኩልነትና ነፃነት እንዳለ እንግሊዛዊቷ ሳቢን ማሊክ ከሪፖርተር ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ገልፀዋል፡፡ የእንግሊዛዊ የእስልምና ሀይማኖት ተከታዮች በኢትዮጵያ በመገኘት የተለያዩ የመንግሥት ባለሥልጣናት፣ ተቃዋሚዎችና የእስልምና እምነት ተከታዮችን አወያይተዋል፡፡
Editorial
Image የሃቀኛ ተፎካካሪ ቤት ተዘግቶ ያድራል!
"የፉክክር ቤት ሳይዘጋ ያድራል" የሚል ምሣሌያዊ አነጋገር አለ፡፡ አንተ ዝጋው፣ የለም አንተ ዝጋው ሲባባሉ የሚዘጋው ጠፍቶ ክፍት ያድራል ለማለትና የስምምነትን ጠቀሜታ ለማጉላት አበው የሚጠቀሙበት ብሂል ነው፡፡

 
Politics
Image በአፍሪካ ቀንድ የኢትዮጵያ ኃያልነት ፈተና
በጌታቸው ንጋቱ

የአሜሪካ መንግስት የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ያለች ኃያል አገር እንደሆነችና በአካባቢው ያለውን የአሜሪካን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበርም ከኢትዮጵያ የተሻለ አማራጭ እንደሌለው ይገለፃል፡፡ በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ቀውሶችን ለመቆጣጠርም ኢትዮጵያ የተሻለች ብቻ ሳትሆን ብቸኛ አማራጭ እንደሆነች የተለያዩ ፀሐፍትና መንግስታት እምነታቸውን ግልጽነት የኢትዮጵያ ኃያልነት በመንተራስ ነው፡፡

Briefs
ደቡብ አፍሪካ ለሱዳን የሰብዓዊ...

ደቡብ አፍሪካ ለሱዳን የሰብዓዊ እርዳታ ልትሰጥ ነው

የደቡብ አፍሪካ መንግስት በአቢይ ክልል ለሚገኙ ሱዳናውያኖች 40 ቶን የሚመዝን ድንኳን፣ ብርድልብስ፣ የወባ መከላከያ አጎበር፣ ፍራሽ፣ ምግብና ልብሶች እርዳታ ሊሰጥ ነው፡፡

 

 
Business & Economy
Image የመንግሥት ግምጃ ቤት ሰነድ ጉዳቱና ጥቅሙ
በብርሃኑ ፈቃደ

"የመንግሥት ግምጃ ቤት ሰነድ ሽያጭ ማስታወቂያ" በየጊዜው በቴሌቪዥን በጋዜጣና በተለያዩ ሚዲያዎች እንመለከታለን፡፡ የግምጃ ቤት ሰነድ ማለት መንግሥት የበጀት ጉድለትን ለመሸፈን የሚጠቀምበት የአጭር ጊዜ ብድር እንደሆነ ከብሔራዊ ባንክ ያገኘነው መረጃ ያስረዳል፡፡ ስለ ጉዳዩ ያናገርናቸው የተወካዮች ምክር ቤት አባልና በኒው ጄኔሬሽን ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ መምህር የሆኑት አቶ ተመስገን ዘውዴ ሲያብራሩ መንግሥት የገንዘብ ፖሊሲውን ለመቆጣጠር ሕዝብን አሳታፊ በሆነ መንገድ የሚጠቀምበት መሣሪያ ነው፡፡

Shemach
ለማረጋጋት ሸማችም ይተባበር
በናታን ዳዊት

ከሸመታና አገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ብዙውን ጊዜ እጃችንን የምንጠቁመው አገልግሎት ሰጪውና ነጋዴው ላይነው፡፡ ይህም የሚሆንበት ዋነኛ ምክንያት በሸማቾች ላይ የሚደርሰውን ሁሉ አቀፍ በደል ይበልጡኑ እነዚህ የሚፈፅሙት በመሆኑ ነው፡፡ ከእነዚህ ሌላ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ለችግሩ መባባስ እጃቸውን የሚያስገቡ አካላት የሉም ማለት አይቻልም፡፡

 
Interview
Image "በእኛ አገር እውቀት እንደ...

"በእኛ አገር እውቀት እንደ ገንዘብ እየተቆጠረ አይደለም"
ካፒቴን መኮንን ሃብት ይመር

ካፒቴን መኮንን ሃብት ይመር ኢኮ የሁሉነሽ የጋዝ ምድጃዎችና የእርሻ መሣሪያ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ድርጅት ባለቤትና ሥራ አስኪያጅ ናቸው፡፡ ኢኮ የሁሉነሽ የነጭ ጋዝ ምድጃን በማምረት ላይ ይገኛሉ፡፡

 

Fermata
የማትሞት ባንዲራ
ይህች ሰንደቅ ዓላማ ትኑር ተጊያጊጣ፣
የአንድነት ማተብ ናት ክፉ ቀን ሲመጣ፡፡
ዘለዓለም ሐዲስ ናት አታውቅም እርጅና፣
እግዜር ነው የሠራት በራሱ ልቡና፣
ከማርያም መቀነት ከቀስተ ደመና፡፡
 
Kibur Minister
ክቡር ሚኒስትር
(ክቡር ሚኒስትሩ የኢትዮጵያን በጐ ገፅታ ለማንፀባረቅ የተቋቋመው የከፍተኛ ባለሥልጣኖች ኮሚቴ አባል ሆነው ከኤክስፐርታቸው ጋር በተለያዩ አገሮች እየተዘዋወሩ ናቸው፡፡ የአውሮፓን ጉዞ ጨርሰው አሁን በአሜሪካ ይገኛሉ፡፡)
Life & Art
"ቡሔ መጣ ያ መላጣ"
በሔኖክ ያሬድ

"መጣና ባመቱ ኧረ እንደምን ሰነበቱ
ክፈትልኝ በሩን የጌታዬን፣
ሆይዬሽ ሎሚታ
ልምጣ ወይ ወደ ማታ
ክፈት በለው ተነሣ ያንን አንበሳ"
 
Social
Image የሚቆጠብ ባይኖርም ይቆጠባል

በምሕረት አስቻለው

ለረዥም ዓመታት ከክፍለ ሀገር ቅቤ፣ አይብና እህል እያመጡ ይነግዱ ነበር፡፡ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ግን እቃዎች ስለተወደዱባቸው ወደ ጉሊት ችርቻሮ ንግድ መግባታቸውን ይናገራሉ ወ/ሮ ፋንቱ ብዙነህ፡

 

Science & Technology
Image የተራቀቁ ሌቦች ለቤጂንግ...

የተራቀቁ ሌቦች ለቤጂንግ ኦሊምፒክ አስግተዋል

የቤጂንግ ኦሊምፒክ በኤሌክትሮኒክስ ወንጀል ለሚፈጽሙ ሰዎች የተጋለጠ መሆኑን የደህንነት ድርጅቶች ማስታወቃቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

 

 
Diaspora
Image ዲያስፖራው በአገሩ ልማት...
ዲያስፖራው በአገሩ ልማት የሚያደርገው እንቅስቃሴ እየተሻሻለ ነው

በምሕረት ሞገስ

ዲያስፖራው ከቁጥሩና ከእውቀቱ አንፃር ወደ አገሩ የገባውና በልማቱ የተሳተፈው ቁጥር አነስተኛ የነበረ ቢሆንም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ቁጥሩ እያደገና በልማቱም የመሰማራት ሁኔታው እየተስፋፋ መሆኑ ተገልጿል፡፡

Youth
Image የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚዋ

በምሕረት አስቻለው

"ማጥናት ለእኔ እንደመዝናናት ነው፡፡ እለት በዕለት የተማርኩትን አጠናለሁ፡፡ ደብተሬ ጠርዝ ላይ ዋና ዋና ነጥቡን እጽፋለሁ፡፡ ቋሚ ጓደኛዬ የምለው በግቢ ውስጥ የለኝም፡፡ በአጋጣሚ ካገኘሁት ተማሪ ጋር እሆናለሁ፡፡ አብዛኛውን ጊዜ የጠበቀ ግንኙነት በትምህርትና በጥናት ሁኔታ ላይ ተፅእኖ ያሳድራል፡፡ የዚያ ዓይነት ግንኙነት የለኝም፡፡ ይህ ለውጤቴ ትልቅ አስተዋፅዖ አድርጓል" ያለችን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አራት ነጥብ በማምጣት ከሥነ ኤዱኬሽን ኮሌጅ የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ የሆነችው ወጣት ማስተዋል መኮንን ነች፡፡

 

 
Opinion
Image ኦሊምፒክን በቲቪ፣ ኢ ቲቪን በኦሊምፒክ

ከበደ አስቻለው

የኦሎምፒክ ጨዋታዎችና ውድድሮች በሬዲዮ ወይም በቴሌቪዥን መሰራጨት እስኪጀመር ድረስ የኦሊምፒክ ንቅናቄ ከአርባ ዓመት በላይ እድሜ አስቆጥሯል፡፡ የመጀመሪያው የ1896 የአቴንስ የኦሊምፒክስ ጨዋታዎች የተዘገቡትና ዜናቸው የተሰማው በጋዜጣና በጋዜጦች ብቻ ነበር፡፡ የወቅቱ ሪከርዶች እንደሚያመላክቱት ለአቴንስ ውድድር እውቅና ያገኙት (አክሬዲት የተደረጉት) ጋዜጠኞች በጣት የሚቆጠሩ ብቻ ነበሩ፡፡

 

Letter to Reporter
በፉክክር ሳይዘጋ ያደረው የፌዴሬሽኑ ቤት
ለሕግ የበላይነት ተገዢ አለመሆን ሥርዓተ አልበኝነትንና ሕገ ወጥነትን ያሰፍናል፡፡ ይህ ዓይነቱ አካሄድ ደግሞ በአገር ውስጥም ሆነ በውጪ ተቀባይነት የለውም፡፡ ከዚህ አኳያ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ፌዴሬሽን (ፊፋ) ያሳለፈውን ውሳኔ ላለመቀበል ሲያመነታ ይታያል፡፡ ማመንታቱ ተቀባይነት የሚያገኝ ቢሆን ኖሮ ባልከፋም ነበር፡፡ ነገር ግን የሚቻል አልመሰለኝም፡፡

 
Women
የአካል ጉዳተኛ ሴቶች ገጠመኝ በምሕረት አስቻለው

"በተለያየ ቦታ ሰዎች ቆንጆ ልጅ ነበረች፤ በማለት ሲናገሩ እሰማለሁ፡፡ እኔም ነኝ ብዬ እመልስላቸዋለሁ፡፡ ነበረች፤ የሚሉት አካል ጉዳተኛ ስለሆንኩ ነው፡፡ የአካል ጉዳተኛ የእለት ከእለት ሕይወት በገጠመኝ የተሞላ ነው፡፡ ልጃገረድ ነሽ? ወሲብ መፈፀም ትችያለሽ? የሚሉ ጥያቄዎችን በተደጋጋሚ ተጠይቄአለሁ፡፡ እነዚህ ለብዙ አካል ጉዳተኛ ሴቶች የሚቀርቡ ጥያቄዎች ናቸው፡፡" ትላለች የሃያ ሦስት ዓመቷ ወጣት ኤልሳቤጥ ንጉሴ፡፡

 

 

Temuaget
ፍርድ ቤት ምን ያህል...

ፍርድ ቤት ምን ያህል ይናገራል? ያናግራልስ?

የመንግሥት መሠረታዊና ዋና ዋና ሥልጣኖች የህግ አውጭነት፣ የህግ አስፈጻሚነት እና የዳኝነት ስልጣኖች መሆናቸው ይታወቃል፡፡ አንዱን የመንግሥት ዓይነት ከሌላው የመንግሥት ዓይነት የሚለየው የተጠቀሱት መሠረታዊ ስልጣኖች ተጠቅልለው፣ ጨርሰውና አካተው በአንድ ሉዓላዊ የሥልጣን አካል እጅ መግባታቸው ወይም መውደቃቸው፣ አለዚያም እነዚህ የመንግሥት መሰረታዊ ሥልጣኖች ሊለያዩና ለየቅልና እኩል ለሆኑ ሦስት የሥልጣን አካላት መደላደላቸው ነው፡፡ እንደ አሜሪካ ባለ ኘሬዚዳንታዊ የመንግሥት ሥርዓት የመንግሥት የህግ አውጭዎች፣ የህግ አስፈጻሚነት የዳኝነት ሥልጣን እንደቅደም ተከተላቸው ለፓርላማ፣ ለኘሬዚዳንቱ (እና ለካቢኔው) እንዲሁም ለፍርድ በት የተሰጡ በመሆናቸው ከዚህ በመነጨ አሰራር በተለይም የዳኝነቱ አካል ሦስተኛው ዘርፍ (ዘ ሰርድ ብራንች) ይባላል፡፡

 

 
Law
የኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ህግ...

የኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ህግ ከወረቀት ዘሏልን?
በሠለሞን ጎሹ

በድምቀት እየተካሄደ ቆይቶ ዛሬ የሚጠናቀቀው የቤጂንግ ኦሎምፒክ ከመጀመሩ በፊት ቻይና ለአካባቢ ጥበቃ የምትሰጠው ትኩረት የላላ መሆኑን በማንሳት ምዕራባዊያኑ መገናኛ ብዙሀን ውርጅብኝ ሲያወርዱባት ነበር፡፡ ቻይና በቅርብ ዓመታት በኢኮኖሚው ረገድ ያደረገችው እምርታ ዜጎቿ በንፁህና ጤናማ አካባቢ ለመኖር እንዲችሉ ባለማድረጉ በርካታ ጥያቄዎች እየተነሱባት ይገኛሉ፡፡ የቻይና በቴክኖሎጂ መራቀቅ ለአካባቢ ጥበቃ ዋስትና የሚሰጥበት ስርዓት እስካልዘረጋ ድረስ ጥያቄዎቹ ወደፊትም ይቀጥላሉ፡፡

 

Zennk
የራስ ጥላ
ማንም በሌለበት . . .
ፀጥ ባለ ምሽት - ለወክ ወጣሁና
እኔና እኔ ሆነን - ሃሳብ ጀመርንና
አንደኛው እኔነት - ከአቅሜ በላይ ሆነ
ሌላኛውን እኔን - ዘርሮ ጣለና
በእኔ ላይ ጀገነ
 
Delalaw
ሕልምና ቅዠት
ሕልምና ቅዠት መለየት ተሳነኝ፡፡ ከዓመታት በፊት ለእውነት ብለው የተሰው፣ የሆድ ዕቃቸውን በንዴት ጠብሰው የተለዩን ሰዎች ድምፅ ተሰማኝ፡፡ ለእውነት ተወልደው፣ ለእውነት ያደጉ ለእምነታቸው የበረቱ ሰዎች፡፡ አእምሮዬ ላይ ..ኢንፍሌሽን.. የሚል ቃል ደወለ፡፡ እኔ በሚስማማኝ መንገድ ተረጎምኩት፡፡ የዋጋ ኢንፍሌሽን፣ የፍቅር ማጣት ኢንፍሌሽን፣ የንቅዘት ኢንፍሌሽን...፡፡

Teles
"በመገለሌ እጄ አጠረ"

በምሕረት ሞገስ

ዛሬ እንደቀድሞው በተበላሹ መኪኖች ሥር እየተንከባለለ አይሠራም፡፡ የመካኒክነት ሥራውን ተወት አድርጐ ሞባይሉንና መፅሐፍ ቅዱሱን በጥቁር ቦርሳው አዝሎ በየመንገዱ ይዘዋወራል፡፡

 

 
Sport
በጥቂት አትሌቶች የቆመ ፌዴሬሽን

29ኛው ኦሊምፒያድ በዓይነቱና በይዘቱ ለየት ያለ ነው፡፡ በቤጂንግ ሲካሄድ ለሰነበተው የቤጂንግ ኦሊምፒክ ቻይናውያን ልዩ ድምቀትን የሰጡት በዝግጅቱ ብቻ ሳይሆን በኦሊምፒክ ጨዋታዎች የበላይነታቸውን ጭምር ማረጋገጣቸው ስለስኬታቸው እንድናስብ እንገደዳለን፡፡

 

Taxi
የቁራ ጩኸት
ከጥቂት ወራት በፊት ኮድ 3 ሚኒባሶች ከአዲስ አበባ የታክሲ ሥራ እንዲወጡ ታዘዙ፡፡ ተጠቃሚው በመውጣታቸው ደስተኛ አልነበረም፡፡ የአዲስ አበባን የትራንስፖርት እጥረት ሳይቃለል እነሱን ከሥምሪት ማስወጣት በሰው ቁስል ላይ እንጨት እንደመስደድ ነው ያሉም ነበሩ፡፡ በትራንስፖርት ባለሥልጣን በኩል የተገልጋዩ ሮሮ ተቀባይነት ስላላገኘ ኮድ ሦስቶች እንደወጡ ቀርተዋል፡፡
 
World
ሩሲያ በፖላንድ ላይ የኒዩክሌር...

ሩሲያ በፖላንድ ላይ የኒዩክሌር ጥቃት እንደምትፈጽም አስታወቀች

የዩናይትድ ስቴትስና የፖላንድ የፀረ ሚሳኤል ግንባታ ስምምነት አዲስ የጦር መሳሪያ እሽቅድምድም እንደሚፈጥር ያስጠነቀቀችው ሩሲያ በፖላንድ ላይ የኒዩክሌር ጥቃት ልትፈጽም እንደምትችል አስታውቃለች፡፡

 

 
  • Do You Know ?
    How To Increase Font Size
    You can increase the font size of the website if it appears smaller than normal. Just click the member area link at the top right of this page and the page will slide down. At the top left corner of the page, look for three small buttons. To increase font size, click the button with "+" sign and "-" sign to decrease font size.
  • Tips !
    Tips for Amharic Version
    • Use Internet Explorer version 6 or better
    • Adjust your screen resolution to 1024 X 768
    • Use the font resizer to increase font size if needed
    • Though it is not strictly needed having power geez unicode font could enhance the font rendering in your browser
 

Important Links

Visit Ethiopian Yellow PagesA forum on Dialogue, Democracy & Development