|
Sunday, 09 March 2008 |
|
በረቡዕ የካቲት 26 ቀን 2000 በፖለቲካ ገጽ ላይ ከአቶ ግርማይ ሃደራ ጋር ያደረጋችሁትን ቃለ መጠይቅ በደንብ አነበብኩትና የሚከተለውን ለማለት ፈለግኩ፡፡
አቶ ግርማይ እንዳሉት አራት ፓርቲዎች፤ የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ኅብረት፣ የኢትዮጵያ ብሄራዊ አንድነት ፓርቲ፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ኃይሎች አንድነት እና የኦሮሞ ነፃነት ብሔራዊ ፓርቲ ግንባር ፈጥረዋል፡፡ በእርግጥ ግንባር መፍጠሩ የሚበረታታ ሲሆን የኢትዮጵያ የፖለቲካ ኃይሎች ከተናጥል ይልቅ በጋራ ቢታገሉ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ ያስችላል፡፡ ነገር ግን ካለፉት ጥምረቶች በመነሳት ምን እናድርግ? እንዴት እንሂድ? ብለው ካለፉት ጥምረቶች ተገቢ ትምህርት መቅሰም አለባቸው፡፡ አቶ ግርማይ ግን ከዚህ በተቃራኒ ካለፉት ጥምረቶች ወይም ኅብረቶች ምንም አንማርም ማለታቸው ቅር አሰኝቶኛል፡፡ ምክንያቱም ከውድቀትም ብዙ መማር ይቻላልና፡፡ ለውድቀታቸው ምክንያት ምን ነበር ብሎ ያንን ላለመድገም ይበጃልና፡፡
(ጎሣዬ ዋቆ፣ ከቡራዩ) |