Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Friday
Jul 04th
Home arrow Sections arrow የከበደ ሚካኤል ግጥም በሥዕል ቀረበ
የከበደ ሚካኤል ግጥም በሥዕል ቀረበ Print E-mail
Sunday, 09 March 2008
የደራሲ ከበደ ሚካኤል አንዱ የግጥም ሥራ ለልጆች በሚመች መልኩ በሥዕል ተቀናጅቶ ለሕትመት በቃ፡፡
“የዕንቁላሉ ተረት በግጥምና በሥዕል” በሚል ርእስ የቀረበው መጽሐፍ ቀደም ሲል “ብርሃነ ኅሊና” ከተሰኘው የግጥም መድበል ደራሲው “ምስጢርና ወሬ” በሚል ርእስ የጻፉት ነው፡፡

በዋሸራ አሳታሚዎች በቅርቡ ስለታተመው መጽሐፍ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህር ዶ/ር ኃይሉ ሃብቱ እንደገለጹት መጽሐፉ የአሁን መልኩን ከመያዙ በፊት ቀድሞ ለአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተሰራጭቶ የአማርኛ ንባብ መልመጃ እንደነበረና ብዙ የዘመኑ ተማሪዎች ሊገለገሉበት፣ እውቀትን ሊገበዩበት፣ የሥነ ምግባር እሴቶችን ሊቀስሙበት እንዲሁም ግጥሞቹን በቃላቸው አጥንተው ሊዝናኑበት በቅተዋል፡፡

በ1994 ዓ.ም. በደራሲ ሐዲስ ዓለማየሁ “ተረት ተረት የመሠረት” መጽሐፍ፣ “የወለደውን የማያከብር፣ የሚያከብረው ልጅ አያገኝም” የሚለውን አንዱን ተረት በሥዕል ተደግፎ በዛምራ አሳታሚ መታተሙ ይታወቃል፡፡

በሔኖክ ያሬድ
 
< Prev   Next >