| ዶ/ር አሸብር ተዘረፉ |
|
|
| Wednesday, 12 March 2008 | |
![]() ዶክተር አሸብር ወልደ ጊዮርጊስ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መስቀል አደባባይ ቅርንጫፍ በቼክ ቁጥር እ.ኤአ CD4886661 በ10/03/08 27,500 ብር፣ በቼክ ቁጥር CD4886662 እ.ኤ.አ በ05/03/08 28,100 ብር በተመሳሳይ ቼክና ፊርማ መዘረፋቸውን ዶክተር አሸብር ገልፀዋል፡፡ "የተዘረፍኩበት ቼክ ሳይቆረጥ በእጄ ይገኛል፡፡ እንዴት ተመሳሳይ ቼክ ተሰራ? ማን ሰራው?" የሚለው ጥያቄ መልስ እስኪያገኝ ጉዳዩ አሳሳቢ እንደሚሆንባቸው ዶክተር አሸብር ተናግረዋል፡፡ ባንኩ እ.ኤ.አ በ10/03/08 በድጋሚ 27"500 ብር ከሰጠ በ31 በበነጋታው ቼክ መስጠታቸውን መጠየቁን፣ እሳቸውም ምንም ዓይነት ቼክ አለመቁረጣቸውን ከገለፁ በኋላ መዘረፋቸውን እንዳወቁ ዶክተሩ አስታውቀዋል፡፡ "ያለምንም ወለድ ንግድ ባንክ የማስቀምጠው ለአስተማማኝነቱ ብዬ ነው" በማለት ባንኩን ያማረሩት ዶክተር አሸብር አጠቃላይ የባንክ ዝርዝር ሂሳብ መግለጫ ሲሰራ የተዘረፉትን ብር መጠን እንደሚያውቁት አመልክተዋል፡፡ የባንኩ ሥራ አስኪያጅ አቶ ንጉሴ ደመቀ ከዶክተር አሸብር ሂሳብ ገንዘብ መዘረፉን አረጋግጠዋል፡፡ ይሁን እንጂ ጉዳዩ በምርመራ ላይ ስለሆነ ባንኩ ዝርዝር መግለጫ ለመስጠት እንደሚቸገር ተናግረዋል፡፡ በአሰግድ ተፈራ |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Forums |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Contact Us |