Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version

Sunday
Jul 05th
Home
You are not authorised to view this resource.
You need to login.
Headline
  • Pause
  • Previous
  • Next
1/10
ምርጫ ቦርድ ለፖለቲካ ፓርቲዎች...

ምርጫ ቦርድ ለፖለቲካ ፓርቲዎች የፋይናንስ ድጋፍ የበጀት ረቂቅ አቀረበ
በፍሬው አበበ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለፓርቲዎች የፋይናንስ ድጎማ የሚውል የበጀት ቀመር አዘጋጅቶ ለመንግሥት ማቅረቡን አስታወቀ፡፡

 

Read more...
 
Zena
"ኢትዮጵያ በኃይል ዘርፉ ራሷን...

"ኢትዮጵያ በኃይል ዘርፉ ራሷን እንድትችል አይፈለግም"
አቶ ምሕረት ደበበ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮረፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ
- ለተያዙት ፕሮጀክቶች ከ 12 ቢሊዮን ዶላር በላይ ያስፈልጋል፡፡
- የቻይና መንግሥት አዲስ የኃይል ማመንጫ ሊገነባ ነው

በአሰግድ ተፈራ

 

Editorial
የኢሕአዴግ መንግሥት፡-...

የኢሕአዴግ መንግሥት፡-
አጠቃላይ የጤና ምርመራ ያስፈልገዋል
"ሰርቪስ" መደረግ አለበት


በአሁኑ ጊዜ ኢሕአዴግ እንደ ፓርቲም ሆነ ስልጣን ላይ እንዳለ መንግሥት እያደረገው ያለው እንቅስቃሴ የጤና ጉድለት ምልክቶች እየታዩበት ነው፡፡ እየታዩ ባሉት የጤና ጉድለቶች ወይም የበሽታ ምልክቶች በአግባቡ የተሟላ ምርመራ ተካሂዶባቸው ተገቢውን ሕክምና ካላገኙ ለራሱም፣ ለአካባቢውም፣ ለአገሪቱም ጠንቅ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ወይም ደግሞ በመካኒካል ቋንቋ እንነጋገር ከተባለ ኢሕአዴግ "ሰርቪስ" መደረግ አለበት፡፡ "ለቦሎ" ተብሎ ሳይሆን ሳይዝግና ሳይቆም መሽከርከር እንዲችልና በሌሎች ተሽከርካሪዎችና መንገዶች ላይም ጉዳት እንዳያደርስ ነው፡፡

 

 
Politics
"በምርጫው የህወሓት አጃቢ...

"በምርጫው የህወሓት አጃቢ ለመሆን አንሳተፍም"
አቶ ገብሩ አስራት
በየማነ ናግሽ

ዓረና ትግራይ፣ የክልሉ ገዢ ፓርቲ ህወሓት እየፈፀመበት ያለው አፈና እና ፀረ ሕገ መንግስታዊ እንቅስቃሴ የማይቆም ከሆነ ፓርቲው ምርጫውን ለማጀብ ብቻ ሊሳተፍ እንደማይችል አሳሰበ፡፡

 

Briefs
የኢትዮጵያ አየር መንገድ... የኢትዮጵያ አየር መንገድ 50 ቴክኒሺያኖችን አስመረቀ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለሁለት ዓመታት በአውሮፕላን ጥገና ያሰለጠናቸውን 50 ቴክኒሻኖችን በዲፕሎማ አስመረቀ፡፡
 
Business & Economy
"በኛ በኩል ፈተና ውስጥ ገብተናል"

አቶ ካሣሁን ፎሎ የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት

አቶ ካሣሁን ፎሎ የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ፕሬዚዳንት ናቸው፡፡ የኤሌክትሪክ ኃይል እጥረት ሠራተኛው ላይ ስላሳደረው ተፅዕኖና በተያያዙ ጉዳዮች ዙሪያ ዳዊት ታዬ አነጋግሯቸዋል፡፡

 

Shemach
የሲሚንቶ ነገር

በናታን ዳዊት

በተደጋጋሚ እንደተነገረውና ሁላችንም በየእለቱ እንቅስቃሴያችን ላይ እንደምናየው የኤሌክትሪክ ሃይል እጥረቱ የፈጠረው ቀውስ የእያንዳንዱን ቤት አንኳኩቷል፡፡ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ እሴቶቻችንንም እያናጋ ነው፡፡ ከሃይል እጥረቱ ጋር በተያያዘ አልተጎዳሁም አልተነካሁም የሚል የለም፡፡

 

 
Interview
"የችግሩ ስር መሰረት ከሆንኩ...

"የችግሩ ስር መሰረት ከሆንኩ ከኃላፊነቴ ለምን አልለቅ""

አቶ ምህረት ደበበ፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ

በአገር አቀፍ ደረጃ በተፈጠረው የኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጥ ሳቢያ የኢትዮጵያ አሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ከፍተኛ ወቀሳ እየተሰነዘረበት ነው፡፡ መንግሥት ችግሩን ወደ ዓለም አቀፍ አበዳሪ ተቋማት ቢመራውም የማይቀበሉ ወገኖች አሉ፡፡ በአጠቃላይ ችግሩና እየተሰራ ስላለው ሥራ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ የሆኑትን አቶ ምህረት ደበበን አሰግድ ተፈራ አነጋግሯቸዋል፡፡

 

Fermata
Image ኦሊምፒክ

ኢንተርናሽናል ኦሊምፒክ ኮሚቴ እ.ኤ.አ. ሰኔ 16 ቀን 1894 ዓ.ም. የእንግሊዝ፣ የአሜሪካ፣ የሶቪየት ሕብረት፣ የሀንጋሪና የግሪክ ተወካዮች በተገኙበት በሳርቦን ዩኒቨርስቲ በተደረገው ኮንግረስ በአማተሪዝም ፍልስፍና ላይ የተገነባ ዓለም አቀፍ ኮሚቴ ሆኖ ተቋቋመ፡፡ የኦሊምፒክ እንቅስቃሴ መሥራች በሆነችው በግሪክ አገር በአቴንስ ከተማ በመሆን በ1896 ተካሄደ፡፡

 

 
Kibur Minister
ክቡር ሚኒስትር

- ትለቃለህ እንዴ?
- ምንድን ነው የምለቀው?
- ከስልጣንህ ከሚኒስትርነትህ
- ለምን? ምነው ጠየቅሽኝ?
- ይህን ጋዜጣ ሳነብ ይኸው "እንደኔ. . . በቃኝ" ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ
- ውድ ባለቤቴ አታስቢ አልለቅም፡፡ ቻው በጧት የሚጀመር ስብሰባ ስላለብኝ ልሂድ

 

Life & Art
"ዝ ተማሪ" እና "ሊቁ"

በሔኖክ ያሬድ

1) ሀ-ሁ-ሂ-ሃ-ሄ-ህ-ሆ፡፡
2) ሀ ግእዝ፣ ሁ ካዕብ፣ ሂ ሣልስ፣ ሃ ራብዕ፣ ሄ ሃምስ፣ ህ ሳድስ፣ ሆ ሳብዕ፡፡
3) አ-ቡ-ጊ-ዳ-ሄ-ው-ዞ፡፡
4) መ-ል-እ-ክ-ተ
5) መልእክተ ዮሐንስ ሐዋርያ ወልደ ዘብዴዎስ ቀዳማዊ ንዜንወክሙ

 
Social
አሰሪዎች ሰራተኞቻቸውን በትዕግስት...

አሰሪዎች ሰራተኞቻቸውን በትዕግስት እንዲይዙ ተጠየቀ
በምሕረት ሞገስ

በኤሌክትሪክ ኃይል እጥረት ሳቢያ አሰሪዎችና አምራች ድርጅቶች ሰራተኞቻቸውን እንዳይቀንሱ ወይም ከሥራ እንዳያሰናብቱ ተጠየቀ፡፡

 

Science & Technology
Image የአሳማ ጉንፋን መድሃኒቱን...

የአሳማ ጉንፋን መድሃኒቱን መለማመዱ ተጠቆመ

ኤክስፐርቶች የአሳማ ጉንፋን (ስዋይን ፍሉ) ወረርሽኝን ለመዋጋት በዋናነት የሚሰጠውን ታሚፍሉ (Tamiflu) መድሃኒት የተለማመደ ስዋይን ፍሉ ማግኘታቸውን አስታወቁ፡፡

 

 
Diaspora
"አንዳንዴ እሠራለሁ የምለው ነገር...

"አንዳንዴ እሠራለሁ የምለው ነገር የህልም ሩጫ ይሆንብኛል"
በምሕረት ሞገስ

"ቤት ማግኘት በጣም አስቸጋሪ ነው፡፡ ብዙ ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው ለመግባትና ለመሥራት ፍላጎት አላቸው፡፡ ነገር ግን የተመቻቸ ነገር የለም፡፡ ቤት ከሌለ እንዴት ይመጣሉ፡፡ ውጭ የነበራቸውን የተደላደለ ኑሮ አፍርሰው መምጣት ይከብዳቸዋል፡፡"

 

Youth
Image አለመቀራረብ
በምሕረት አስቻለው

ታላላቆቹ ቀደም ሲል የፋይል ማቀፊያ (box file) እየሰሩ ራሳቸውን ይደግፉ ቤተሰቦቻቸውንም ይረዱ እንደነበር ነግሮናል የአስራ ዘጠኝ ዓመቱ ወጣት እዮብ ካሳሁን፡፡ የሚኖረው አራት ኪሎ 15/16 ቀበሌ ውስጥ ነው፡፡
 
Opinion
የራስን መብትና ጥቅም...

የራስን መብትና ጥቅም መወሰን ነውር ነው

በዛብህ ንጉሡ

በ1954 ዓ.ም. ታህሳስ 28 ቀን የፓርላሜንት አማካሪዎችን ደመወዝ ለመወሰን የወጣን አዋጅ በወቅቱ በነበረው ሕገ መንግሥት ሕግና አሰራር መሰረት ንጉሠ ነገስቱ ያወጁት "በተሻሻለው ሕገ መንግሥታችን በአንቀጽ 34፣ 83 እና 88 የተጻፈውን አይተን የሕግ መምሪያና የሕግ መወሰኛ ምክር ቤቶቻችን መክረውበት ያቀረቡልንን ተመልክተንና ፈቅደን ቀጥሎ ያለውን አውጀናል" ብለው ነው፡፡ በዚህም መሰረት የእያንዳንዱ የፓርላሜንት አማካሪ የወር ደመወዝ አምስት መቶ ብር እንዲሆን ተወሰነ፡፡ ፓርላሜንቱ ማለት ወይም በወቅቱ ሥራ ላይ በነበረው የ1948 ዓ.ም. ሕገ መንግሥት መሰረት "ፓርላሜንቱ የሕግ መምሪያ ምክር ቤትንና የሕግ መወሰኛ ምክር ቤትን ይዞ የሚገኝ" ወይም የሚያጠቃልል በመሆኑ የፓርላሜንት አማካሪዎች ደመወዝ አዋጅ ይወጣል በዚህም መሰረት የእያንዳንዱ የፓርላሜንት አማካሪ የወር ደመወዝ አምስት መቶ ብር እንዲሆን የተወሰነ ነው፡፡ ራሱ ፓርላማው ማለትም የሕግ መምሪያና የሕግ መወሰኛ ምክር ቤቶች መክረውበት ነው፡፡

Letter to Reporter
የማን ጥፋት ነው?

ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ፣ ከምርጫ 97 ወዲህ ሥልጣን መልቀቅን በሚመለከት በተለያዩ ጊዜያት ቃለ ምልልስ አድርገዋል፡፡ ሁሉም ቃለ ምልልሶች ያካሄዱት ግን ከውጭ ሚዲያዎች ጋር ነው፡፡ በአገር ውስጥ ሚዲያ የምንሰማው ማስተባበያውን ነው፡፡

 

 
Women
"መጽሐፍ ትልቅ ዋጋ እንዳለው...

"መጽሐፍ ትልቅ ዋጋ እንዳለው የተረዳሁት ለሽልማት ስበቃ ነው"

በትዕግስት ዘሪሁን

ወ/ሮ ሐመረ ታደገ ከ1997 ዓ.ም ጀምሮ በአገር አቀፍ ደረጃ በተቋቋመው የአፈጻጸም ሥራ አመራርና የመሰረታዊ የሥራ ሂደት ለውጥ አማካሪና አስተባባሪ ቡድን ውስጥ በመሥራት ላይ ከሚገኙ ጥቂት ሴቶች አንዷ ናቸው፡፡ የመሰረታዊ የሥራ ሂደት ለውጥ በሚል የቢፒአርን ጽንሰ ሃሳብ እና አተገባበር "የሥራ ሂደት ለውጥ (ቢፒአር"" የሚል መጽሐፍ ተርጉመው አቅርበዋል፡፡ ይህም ለመጀመሪያ ጊዜ የቢፒአርን ጽንሰ ሃሳብ ወደ አማርኛ የተረጎሙ አድርጓቸዋል፡፡ በቢፒአር ጽንሰ ሃሳብና በኛ ሀገር ያለውን አተገባበር በተመለከተ አነጋግረናቸዋል፡፡

Temuaget
ከአስራ ስምንት ዓመት... ከአስራ ስምንት ዓመት በፊት በዚህ ክረምት ውስጥ ርግር እና የ"ሽፍንፍን" ጉባኤ ድግስ
(በቀለ ሹሜ)
1
ግንቦት 20 በስርቆትና በዝምታ ቢጠይምም፣ አንድ ነገር ግን እውነት ነበር - የወታደራዊ አምባገነንነት እንዳይሆን ፈርሶ ነበር፡፡ ፈላጭ ቆራጮች እምቧጮ ሆኑ፡፡ በጊዜ ንብረትና ቤተሰብ አሽሽተው ያመለጡ አመለጡ፡፡ አንዳንዶቹም ሊሸሹ ሞክረው የነበሩ ባልደረቦቻቸውን እስርቤት ከርችመው ጣሊያን ኤምባሲ ተሸጎጡ፡፡ ቀሪዎች መላ ሳያበጁ ነጋባቸው፡፡ ወታደራዊ ሃይላቸው የፀጥታ መረባቸውና ፓርቲያቸው ተበጣጥሷል፡፡ ከሀገር አንድነት ጀርባ የመሸገውና (እነኢህአፓ ጭምር ሲያስቡት የቆዩት) ፀረ ዲሞክራሲያዊ አመለካከታቸውና ፀረ ወያኔ ፕሮፓጋንዳቸው ግን ጫፉም አልተነካም፡፡ የወያኔም ገመና የሚሞቅ ጥሩ ቡልኮ ሆኖ ማገልገሉ አልቀረም፡፡
 
Law
የፍትሕ ሚኒስቴርና የፌዴራል...

የፍትሕ ሚኒስቴርና የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት አለመግባባት

በሰለሞን ጎሹ

የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በቅርቡ በመዝገብ ቁጥር 26127 የተመለከተው ጉዳይ ዋና ጭብጥ ኑሯቸውን አሜሪካን አገር ያደረጉ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ባለትዳር የአሜሪካ ዜጎች በአዲስ አበባ ያላቸው ተንቀሳቃሽ ያልሆነ ንብረት (ቤት) ለማስመለስ ኢትዮጵያዊ ወይዘሮን መክሰስ ላይ ሲሆን፣ ተሰሳሿ ከሳሾቼ ኤርትራዊያን ናቸው፣ ጠበቃቸውም ሕጋዊ ወክልና የላቸውም ሲሉ ተከራክረዋል፡፡ የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ከፍትህ ሚኒስቴር የጠበቆች ዲሲፒሊን ጉባኤ የነሐሴ 16 ቀን 2000 ዓ.ም. ውሳኔ ጋር ቀጥተኛ ተያያዥነት ያለው ሲሆን የጠበቃ ውክልናውን ለማረጋገጥ የተለያዩ ሰነዶችን ከአሜሪካ ሁለት ጊዜ እንዲላኩ ተደርጓል፡፡

 

Zennk
አትላንታ ኦሊምፒክ አትላንታ ኦሊምፒክ እ.ኤ.አ ከሐምሌ 13 ቀን እስከ ነሐሴ 4 ቀን 1996 ተካሂዷል፡፡ በወቅቱ በተካሄደው ኦሊምፒክ ጌምስ የ197 አገሮች 6"797 ወንዶችና 3"523 ሰቶች ተካፍለዋል፡፡ ውድድሮቹን 2 ሚሊዮን ስፖርት አፍቃሪዎች በተለያዩ ስታዲየሞች በመገኘት የተመለከቱት ሲሆን፣ 3.5 ቢሊዮን ሰዎች በቴሌቭዥን ተከታትለውታል፡፡
 
Delalaw
ሆዴ ሽብር ሽብር

ኑሮ አንዳንዴም ሲገለብጠን፣ አንዳንዴም ስንገለብጠው. . .ይኸው አለን፡፡ ደላላው አምበርብር ምን ተስኖት ነኝ፡፡ ማንጠግቦሽ ኑሮ "ኩዴታ" እንዳያካሄድብን ቴክኒኩን ትቆጣጠራለች፡፡ የእኔና የእናንተ ግንኙነት ፍሬያማ እንዲሆን ምክር ትሰጣለች፡፡ አስተያየት ትሰነዝራለች፡፡ አምበርብር ባለበት ማንጠግቦሽ አለች፡፡ ውሻችን ኮራ የቅንጥብጣቢ ዋጋ በመናሩ ሳቢያ ማላዘኑን ጨምሯል፡፡ ዋጋ ሲንር ጩኸት ይጨምራል?

 

Teles
"እርሳኝ"

በትዕግስት ዘሪሁን

የአምስት ወሩ ሕፃን ከአስር ዓመቷ ሕፃን ጀርባ ላይ እንደታዘለ እርር ብሎ ያለቅሳል፡፡ ያዘለችው ሕፃን ከወዲያ ወዲህ እያለች ለማባበል ሞከረች፡፡ አልተሳካላትም፡፡ እርቦት እንደሆነ እናቱ ገብቷታል፡፡ "ከጠባ ቆይቷል፡፡ እርቦት ነው፡፡ እንካ ይቺን ጥባ" አለችና አውራ ጣቱን አጎረሰችው፡፡ ማልቀሱን አላቋርጥ ሲል የሱን ታላቅ በጀርባዋ ያዘለችው እናቱ ዝቅ ብላ ጡቷን አጎረሰችው፡፡

 
Sport
የእግር ኳሱ እጩዎች እነማን ናቸው? በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ውስጥ ተፈጥሮ የቆየው አለመግባባት እልባት አግኝቷል በተባለበት በአሁኑ ሰዓት፣ ሐምሌ 11 ቀን 2001 ዓ.ም. ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አመራር እጩ በቀረቡ ወገኖች ማንነት የተቃውሞ አስተያየቶች በመስማት ላይ ይገኛል፡፡

Taxi
መፍትሔ

"አዳዲስ ታክሲዎች ለምን አይጨመሩም" አለ አንድ ወጣት በትራንስፖርት እጥረት ተማርሮ፡፡ አሁን አሁን አዳዲስ ታክሲዎች አይታዩም፡፡ ሾፌር ምክንያቱን ያውቅ ይሆናል ብሎ የሾፌሩን መልስ ጠበቀ፡፡ እንደሚጠበቅ ያወቀው ሾፌርም ለመልስ ተዘጋጀ፡፡

 

 
World
Image ሆንዱራስ - የመፈንቅለ መንግሥት ሰለባ በኃይሌ ሙሉ

የሆንዱራስ ፕሬዚዳንት በወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ከስልጣን መወገዳቸውን ተከትሎ በፕሬዚዳንቱ ደጋፊዎችና በፀጥታ ኃይሎች መካከል ግጭት ተፈጥሯል፡፡ መፈንቅለ መንግሥቱን ከባራክ ኦባማ እስከ ሁጎ ቻቬዝ ድረስ የበርካታ መንግሥታት መሪዎች ያወገዙት ሲሆን፣ ፕሬዚዳንቱ በአስቸኳይ ወደ ስልጣናቸው እንዲመለሱ ጠይቀዋል፡፡
Fere Kenafir
ፍሬከናፍር
"... ፓርላሜንቱ የአባሎቹን ደመወዝ የሚያሳድግ ማናቸውንም ሕግ ያወጣ
 
  • Advertisement
 

Advertisement

Click here to visit our web site

Got an Idea ?

Share your thought and ideas with others on our public forum. Just register here and participate on our new and improved forum. Note that all members of the old version forum have to register again to post on the new version forum.

www.isynci.com