Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Sunday
Jul 20th
Home arrow Sections arrow የሪል ስቴት ኩባንያዎች ካፒታል...
የሪል ስቴት ኩባንያዎች ካፒታል... Print E-mail
Wednesday, 12 March 2008
የሪል ስቴት ኩባንያዎች ካፒታል ወደ 33.5 ቢሊዮን ብር አደገ

ባሳለፍነው አንድ ዓመት ውስጥ 101.42 ቢሊዮን ብር ካፒታል ካስመዘገቡ 6920 ፕሮጀክቶች ውስጥ በሪልስቴት ለመሰማራት ፈቃድ የወሰዱት ኩባንያዎች ከጠቅላላ ካፒታል ውስጥ አንድ ሶስተኛውን ያዙ፡፡ ለሆቴልና ሬስቶራንት ግንባታ ፈቃድ የወሰዱ ባለሃብቶች ቁጥር በእጥፍ ጨመረ፡፡ 
 
የኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ኤጀንሲ የ2007 እንቅስቃሴውን የሚያመለክተው ሪፖርት ላይ እንደተጠቀሰው በሪልስቴትና ተያያዥ ቢዝነስ ለመሰማራት በአንድ ዓመት ውስጥ ብቻ ፈቃድ የወሰዱ ኩባንያዎች 33.5 ቢሊዮን ብር ካፒታል ማስመዝገብ ችለዋል፡፡

በ2006 በጀት ዓመት ይህ ዘርፍ 21.76 ቢሊዮን ብር በጀት በማስመዝገብ ከፋብሪካዎች ግንባታ ቀጥሎ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ይገኝ እንደነበር ታውቋል፡፡

በ2006 የፋብሪካዎች ግንባታ ዘርፍ 39.22 ቢሊዮን ብር ካፒታል በማስመዝገብ የመጀመሪያ ደረጃን ይዞ እንደነበር የኤጀንሲው መረጃ ያስረዳል፡፡

በ2007 ግን የፋብሪካዎች ግንባታ ዘርፍ ፕሮጀክቶች ቁጥር ቢያድግም ያስመዘገበው ካፒታል 26.6 ቢሊዮን ብር ብቻ በመሆኑ ደረጃውን ለሪልስቴት በመልቀቅ ሁለተኛ ደረጃ እንዲይዝ ሆኗል፡፡

በሪልስቴት የሚሰማሩ ባለሃብቶች ቁጥር ከሌሎች ዘርፎች በበለጠ እያደገ በመምጣቱ በ2007 የበጀት ዓመት ፈቃድ ከተወሰደባቸው ጠቅላላ ፕሮጀክቶች ካስመዘገቡት ካፒታል አንድ ሦስተኛውን እጅ ከመያዛቸውም ሌላ ከሌሎች ዘርፎች በተሻለ መልኩ ወደ ሥራ ገብተዋል፡፡

በአሁኑ ጊዜ በከፍተኛ ደረጃ ላይ አድጐ ትልቅ ፈቃድ የሚወሰድበት የኢንቨስትመንት መስክ የሆነው ሪልስቴት በ1984 ዓ.ም በዚህ ዘርፍ ለመሰማራት ፈቃድ የሰጡት ኩባንያዎች ቁጥር ሦስት ብቻ ነበሩ፡፡ በወቅቱም 17 ሚሊዮን ብር ብቻ ነበር፡፡

ይህ ቁጥር በ1985 ዓ.ም አድጐ የፕሮጀክቱ ብዛት 133 ሊሆን መቻሉንና ኢንቨስትመንቱም 891 ሚሊዮን ብር ማደግ ችሎ አሁን የደረሰበት ደረጃ ሊደርስ ችሏል፡፡

ከሁለቱ ሌላ ለእርሻና ለመሰል ዘርፎች 16.7 ቢሊዮን ብር በሆቴልና በሬስቶራት ግንባታ ለመሰማራት ፈቃድ የወሰዱ ደግሞ 12.8 ቢሊዮን ብር ካፒታል አስመዝግበዋል፡፡

በተለይ በሆቴል ሥራ ለመሰማራት በኢትዮጵያ ይቀየር 474 ፈቃድ የተሰጠ ሲሆን አስመዝግበውት የነበረው ካፒታልም 5.5 ቢሊዮን ብር እንደነበር መረጃው ጠቁሟል፡፡ በ2007 በዚህ ዘርፍ ለመሰማራት ፈቃድ የተሰጣቸው ፕሮጀክቶች ወደ 842 ማደጉንና ካፒታላቸውም ከ12 ቢሊዮን ብር መድረሱ ከሌሎች ዘርፎች ሁሉ በእጥፍ እድገት የታየበት እንዲሆን አድርጎታል፡፡

በአንድ ዓመት ልዩነት ውስጥ በእጥፍ ያደገው የሆቴልና ሬስቶራንት ዘርፍ የኢንቨትመንት ፈቃድ መሰጠት በተጀመረበት 1984 ዓ.ም 54 ለሚሆኑ ፕሮጀክቶች ፈቃድ መሰጠቱንና እነዚህም ፕሮጀክቶች 454 ሚሊዮን ብር እንደነበር ያመለክታል፡፡

መሃከል ላይ ግን በዚህ ዘርፍ በተለይ በ1993 ዓ.ም ፍቃድ የተሰጠው ለ6 ፕሮጀክቶች ሲሆን በ1994 ዓ.ም ሰባት ፕሮጀክቶች ነበሩ ሆኖም ከ1997 ዓ.ም ጀምሮ ቁጥሩ እያደገ በመምጣት በየዓመቱ በአማካይ ከ450 በላይ ለሚሆኑ በሆቴልና በሬስቶራንት ዘርፍ ለመሰማራት ለሚፈልጉ ፍቃድ ተሰጥቷል

በመረጃው መሠረት ቅናሽ ያሳየው በኮንስትራክሽን ዘርፍ የተመዘገበው ካፒታል ነው፡፡ በዚህ ዘርፍ በኢትዮጵያ ይቀየር 4.1 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሃብቶች ፈቃድ የወሰዱ ቢሆንም ግን ወደ 1.87 ቢሊዮን ብር ዝቅ ብሏል፡፡

በኤጀንሲው ዋና ዋና ፈቃድ ከሚሰጥባቸው 15 ከሚሆኑ ዘርፎች ውስጥ እርሻ፣ ኮንስትራክሽን፣ ትምህርት፣ አሳ እርባታ፣ የጤናና ማኅበራዊ አገልግሎት፣ ፋብሪካ ግንባታ፣ ሆቴልና ሬስቶራንት፣ ሪል ስቴት ተጠቃሽ ናቸው፡፡

በዳዊት ታዬ
 
< Prev   Next >