| በአዲሱ የባቡር ሃዲድ ዝርጋታ... |
|
|
| Wednesday, 12 March 2008 | |
|
በአዲሱ የባቡር ሃዲድ ዝርጋታ ለመሳተፍ አንድ የአሜሪካ ኩባንያ ፍላጎት እንዳለው አስታወቀ
ኢትዮጵያ አምስት ሺህ ኪሎ ሜትር ርዝማኔ ያለው የባቡር ሃዲድ ለመዘርጋት ማቀድዋንና ለዚህ ኢንቨስትመንትም አንድ የአሜሪካው ሎጂስቲክ የተባለው ኩባንያ ፍላጎት እንዳለው ማሳወቁን የትራንስፖርትና መገናኛ ሚኒስቴርን ጠቅሶ ሱዳን ትሪቡን ዘግቧል፡፡ እንደዘገባው ከሆነ አዲስ የሚሰራው የባቡር ሐዲስ መስመር ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ቀንድ አገሮች ጋር የሚያገናኝና እምቅ የሃይልና የማዕድን ሃብትን ለመጠቀም የሚያስችል ነው፡፡ የባቡር ሃዲድ መስመሩ ግንባታ በቅርብ ጊዜ ውስጥ እንደሚጀመር የተናገሩት ሚኒስትሩ ከግንባታው መጀመር ቀደም ብሎ የባቡር መስመሩን የሚቆጣጠር ኤጀንሲ እንደሚቋቋም አመልክተዋል፡፡ አገሪቱ ያላትን የተፈጥሮ ሃብት ለመጠቀም በተለይ በምዕራብ ኢትዮጵያ የሚገኘውን የብረት ማዕድን ለማውጣት፣ በምሥራቅ በኩል ደግሞ የጋዝና የነዳጅ ዘይት ሃብቷን ለመጠቀም እንዲሁም ንግድና እርሻን ለማስፋፋት የሚገነባው የባቡር መስመር ትልቅ እገዛ ይኖረዋል ተብሎ ታምኖበታል፡፡ ሚኒስትሩ የባቡር መስመሩን ለመገንባት የሚያስፈልገውን ገንዘብ በተመለከተ ማብራሪያ ያልሰጡ መሆኑን ዘገባው አመልክቷል፡፡ በጋዜጣው ሪፖርተር |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Forums |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Contact Us |